የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የአዳማ ከተማን የኮንፍረንስ ቱሪዝም የስበት ማዕከልነት የሚያጎለብቱ ዲጂታል አሰራሮች ተግባራዊ እየተደረጉ ነው

Jul 3, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2017(ኢዜአ)፦የአዳማ ከተማን የኮንፍረንስ ቱሪዝም የስበት ማዕከልነት የሚያጎለብቱ የዲጂታል አሰራሮች ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን የከተማዋ ቱሪዝም ኮሚሽን ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

በከተማዋ የሚገኙ ሆቴሎችም ከተማ አስተዳደሩ አበረታች ድጋፍ እያደረገላቸው መሆኑን ገልጸዋል።

ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ መንግስት ለቱሪዝም ዘርፉ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ከአምስቱ የኢኮኖሚ ዘርፎች መካከል አንዱ እንዲሆን አድርጓል።

ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ የኮንፍረንስ ቱሪዝም በኢትዮጵያ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ ይገኛል።

ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የአዳማ ከተማ ቱሪዝም ኮሚሽን ጽህፈት ቤት ሀላፊ ተስፋዬ ጎሳዬ አዳማ በኮንፍረንስ ቱሪዝም እያደጉ ከመጡ ከተሞች መካከል ተጠቃሽ መሆኗን ገልጸዋል።


የተለያዩ ስብሰባዎች እና ስልጠናዎች በአዳማ ከተማ እንደሚካሄዱ ጠቁመው፤ በከተማዋ ያሉ ሆቴሎችም ለስብሰባም ሆነ ለማረፊያነት የሚያገለግሉ ደረጃቸውን የጠበቁ አገልግሎቶች እየሰጡ እንደሚገኙ አንስተዋል።

ለዚህም ቱሪስቶች የሚያርፉባቸው 62 ደረጃቸውን የጠበቁ ሆቴሎች መኖራቸውንና በአጠቃላይ 220 የሚጠጉ ሆቴሎች መኖራቸውን ገልጸው፤ በአንድ ጊዜ እስከ 32 ሺህ ሰዎችን የማስተናገድ አቅም መኖሩን ተናግረዋል።

በአዳማ የሚገኙ ሆቴሎች የሚገኙበት ፖርታል መዘጋጀቱን እና ተጨማሪ የኦንላይን፣ ጎግል ማፒንግ እና የሞባይል አፕሊኬሽን ለማልማት ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

እነዚህ ወደ ስራ በሚገቡበት ወቅት የኮንፍረንስ ቱሪዝሙን ሙሉ እንደሚያደርጉት ተናግረዋል።

በተጨማሪም በርካታ ሆቴሎች እየተገነቡ መሆናቸውን ገልጸው፤ ለአብነትም ከ2012 እስከ 2016 ባሉት ጊዜያት 195 ፕሮጀክቶች በዚህ ዘርፍ ፈቃድ ወስደው እየሰሩ እንደሚገኙ ጠቁመዋል።

በከተማዋ በዘርፉ መሰማራት ለሚፈልጉ ከቦታ ጀምሮ በርካታ ማበረታቻዎች እየተሰጡ መሆናቸውን እና አልሚዎች በተፈጠሩ ምቹ ሁኔታዎች እንዲጠቀሙ ጥሪ አቅርበዋል።

የስማርት አዳማ ፕሮግራም ለዘርፉ ዲጂታላይዜሽን ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ጠቁመው፤ የሆቴሎች የሰው ሀይል አስተዳደር በሲስተም እንዲሆን ለማድረግ ጥረቶች እየተደረጉ መሆናቸውን አመላክተዋል።

ይህም ከዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በተናበበ መልኩ እየተሰራበት መሆኑን ጠቁመው፤ በከተማዋ እየተካሄደ ያለው ልማትም ዘርፉን በጉልህ እያሳደገው መሆኑንም ገልጸዋል።

በከተማዋ የሚገኙ ሆቴሎች የስራ ሀላፊዎችም በከተማ አስተዳደሩ ለዘርፉ ተዋናዮች አበረታች ድጋፍ እያደረገላቸው መሆኑን አንስተዋል።




የኮንፍረንስ ቱሪዝምን የሚያጠናክሩ ዘርፈ ብዙ ግልጋሎቶች እየተሰጡ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026