
ወላይታ ሶዶ፤ ሰኔ 25/2017 (ኢዜአ) --በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የህዝቡን ፍትሃዊ የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ገለጹ፡፡
የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት የ2018 ዓ.ም በጀት ማከፋፈያ ቀመር ሂደት ላይ ተግባቦት ለመፍጠር ያለመ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ በወላይታ ሶዶ ከተማ ተካሂዷል፡፡

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ በዚህ ወቅት እንደገለጹት በክልሉ ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍል እና የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት በትኩረት እየተከናወኑ ነው።
የክልሉን ህዝብ አዳጊ ፍላጎቶችን ለማሟላት እና ፍትሃዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በበጀት ቀመር ላይ ተግባቦት መፍጠር እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል።
በዚህም የ2018 ዓ.ም በጀት ከመወሰኑ በፊት ከተለያዩ ምንጮች የተሰበሰቡ መረጃዎችን መሰረት በማድረግ የበጀት ቀመሩን ለመስራት መግባባት ላይ መድረስ በማስፈለጉ መድረኩ መዘጋጀቱን ገልጸዋል።
የክልሉ ብሄረሰቦች ምክር ቤት በበጀት ቀመሩ ላይ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ማከናወኑን ጠቅሰው መግባባት የተደረሰበት መረጃ ለክልሉ ምክር ቤት ይቀርባል ብለዋል፡፡

የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አዳማ ቲምጳዬ በበኩላቸው በ2018 በጀት ዓመት ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍልና የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ መረጃዎችን የማደራጀት ስራ መሰራቱን ገልጸዋል።
መድረኩ በሁሉም መዋቅር አመራሮች ዘንድ ግልጽነትና መግባባት በመፍጠር የኢኮኖሚን አቅምን መሠረት ያደረገ የበጀት ቀመር ተግባራዊ ለማድረግ የሚያግዝ ነው ብለዋል፡፡
ግልጽና ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍል እንዲኖር የ2018 በጀት ቀመር የማዘጋጀትና የማደራጀት ስራ ሲሰራ መቆየቱን የተናገሩት ደግሞ የክልሉ ፕላን እና ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፈቃደስላስ ቤዛ ናቸዉ።
የዘንድሮውን የበጀት ቀመር የማዘጋጀቱ ስራ እየተገባደደ ባለው በጀት ዓመት የተስተዋሉ ችግሮችን በመቅረፍ ለበጀት ቀመር ዝግጅት መረጃዎችን የማናበብና የማጥራት ተግባር የተከናወነበት መሆኑንም ገልጸዋል።
ለዚህም ስራ ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ ያሉ የሶስት ዓመት መረጃዎችን የማመሳከር ስራ መሰራቱንም አክለዋል።
በመድረኩ የክልል፣የዞኖች እና የ3ቱ ሪጂዮፖሊስ ከተሞች ባለድርሻዎች ተገኝተውበታል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025