
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦በመንግስት እና የግል አጋርነት ሜጋ ፕሮጀክቶችን የመፈጸም ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ገለጹ።
ሚኒስትሩ ይህን ያሉት በመንግስትና የግል አጋርነት የሚከናወኑ 7 ፕሮጀክቶች ስምምነት በተፈረሙበት ወቅት ነው።

የተፈረሙ ስምምነቶች አራት የቤት ልማት፣ ሁለት የቱሪዝም መዳረሻዎችንና የጤና መሰረተ ልማት በመንግስትና የግል አጋርነት ማልማት የሚያስችሉ ናቸው ተብሏል።
ኦቪድ ግሩፕ፣ አይሲኢ ዲቨሎፕመንትና ኮንስትራክሽን ድርጅት በቤት ልማት ፕሮጀክት፣ ቦስተን ፓርትነርስና ሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በቱሪዝም መዳረሻ ልማት፣ በሴርባ ላንሴት አፍሪካ እና ዓለም አቀፍ ክሊኒካል ላብራቶሪስ ተግባራዊ የሚደረገው የተቀናጀ የዲያግኖስቲክ አገልግሎት ግንባታ ፕሮጀክት በድርጅቶቹ ሃላፊዎች እና በሚመለከታቸው የመንግስት ተቋማት አመራሮች ተፈርሟል።
የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ በፊርማ ስነስርዓቱ ወቅት እንዳሉት የተደረጉት ስምምነቶች በመንግስት ልዩ ትኩረት የተሰጣቸውን ፕሮጀክቶች በመንግስትና የግል አጋርነት ማከናወን የሚያስችሉ ናቸው።

በቀጣይም ሀገራዊ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን በግልና የመንግስት አጋርነት የመፈጸም ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
የተደረጉት ስምምነቶች የሀገር ውስጥ ባለሀብቶችን በማበረታታት ትልቅ ፋይዳ እንዳላቸው በመጠቆም ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ አሳስበዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025