
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦በመንግስት እና የግል አጋርነት ሜጋ ፕሮጀክቶችን የመፈጸም ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ገለጹ።
ሚኒስትሩ ይህን ያሉት በመንግስትና የግል አጋርነት የሚከናወኑ 7 ፕሮጀክቶች ስምምነት በተፈረሙበት ወቅት ነው።

የተፈረሙ ስምምነቶች አራት የቤት ልማት፣ ሁለት የቱሪዝም መዳረሻዎችንና የጤና መሰረተ ልማት በመንግስትና የግል አጋርነት ማልማት የሚያስችሉ ናቸው ተብሏል።
ኦቪድ ግሩፕ፣ አይሲኢ ዲቨሎፕመንትና ኮንስትራክሽን ድርጅት በቤት ልማት ፕሮጀክት፣ ቦስተን ፓርትነርስና ሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በቱሪዝም መዳረሻ ልማት፣ በሴርባ ላንሴት አፍሪካ እና ዓለም አቀፍ ክሊኒካል ላብራቶሪስ ተግባራዊ የሚደረገው የተቀናጀ የዲያግኖስቲክ አገልግሎት ግንባታ ፕሮጀክት በድርጅቶቹ ሃላፊዎች እና በሚመለከታቸው የመንግስት ተቋማት አመራሮች ተፈርሟል።
የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ በፊርማ ስነስርዓቱ ወቅት እንዳሉት የተደረጉት ስምምነቶች በመንግስት ልዩ ትኩረት የተሰጣቸውን ፕሮጀክቶች በመንግስትና የግል አጋርነት ማከናወን የሚያስችሉ ናቸው።

በቀጣይም ሀገራዊ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን በግልና የመንግስት አጋርነት የመፈጸም ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
የተደረጉት ስምምነቶች የሀገር ውስጥ ባለሀብቶችን በማበረታታት ትልቅ ፋይዳ እንዳላቸው በመጠቆም ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ አሳስበዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026