የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በመንግስት እና የግል አጋርነት ሜጋ ፕሮጀክቶችን የመፈጸም ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል-ሚኒስትር አህመድ ሽዴ

Jul 4, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦በመንግስት እና የግል አጋርነት ሜጋ ፕሮጀክቶችን የመፈጸም ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ገለጹ።

ሚኒስትሩ ይህን ያሉት በመንግስትና የግል አጋርነት የሚከናወኑ 7 ፕሮጀክቶች ስምምነት በተፈረሙበት ወቅት ነው።


የተፈረሙ ስምምነቶች አራት የቤት ልማት፣ ሁለት የቱሪዝም መዳረሻዎችንና የጤና መሰረተ ልማት በመንግስትና የግል አጋርነት ማልማት የሚያስችሉ ናቸው ተብሏል።

ኦቪድ ግሩፕ፣ አይሲኢ ዲቨሎፕመንትና ኮንስትራክሽን ድርጅት በቤት ልማት ፕሮጀክት፣ ቦስተን ፓርትነርስና ሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በቱሪዝም መዳረሻ ልማት፣ በሴርባ ላንሴት አፍሪካ እና ዓለም አቀፍ ክሊኒካል ላብራቶሪስ ተግባራዊ የሚደረገው የተቀናጀ የዲያግኖስቲክ አገልግሎት ግንባታ ፕሮጀክት በድርጅቶቹ ሃላፊዎች እና በሚመለከታቸው የመንግስት ተቋማት አመራሮች ተፈርሟል።

የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ በፊርማ ስነስርዓቱ ወቅት እንዳሉት የተደረጉት ስምምነቶች በመንግስት ልዩ ትኩረት የተሰጣቸውን ፕሮጀክቶች በመንግስትና የግል አጋርነት ማከናወን የሚያስችሉ ናቸው።


በቀጣይም ሀገራዊ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን በግልና የመንግስት አጋርነት የመፈጸም ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

የተደረጉት ስምምነቶች የሀገር ውስጥ ባለሀብቶችን በማበረታታት ትልቅ ፋይዳ እንዳላቸው በመጠቆም ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026