
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦በመንግስት እና የግል አጋርነት ሜጋ ፕሮጀክቶችን የመፈጸም ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ገለጹ።
ሚኒስትሩ ይህን ያሉት በመንግስትና የግል አጋርነት የሚከናወኑ 7 ፕሮጀክቶች ስምምነት በተፈረሙበት ወቅት ነው።

የተፈረሙ ስምምነቶች አራት የቤት ልማት፣ ሁለት የቱሪዝም መዳረሻዎችንና የጤና መሰረተ ልማት በመንግስትና የግል አጋርነት ማልማት የሚያስችሉ ናቸው ተብሏል።
ኦቪድ ግሩፕ፣ አይሲኢ ዲቨሎፕመንትና ኮንስትራክሽን ድርጅት በቤት ልማት ፕሮጀክት፣ ቦስተን ፓርትነርስና ሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በቱሪዝም መዳረሻ ልማት፣ በሴርባ ላንሴት አፍሪካ እና ዓለም አቀፍ ክሊኒካል ላብራቶሪስ ተግባራዊ የሚደረገው የተቀናጀ የዲያግኖስቲክ አገልግሎት ግንባታ ፕሮጀክት በድርጅቶቹ ሃላፊዎች እና በሚመለከታቸው የመንግስት ተቋማት አመራሮች ተፈርሟል።
የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ በፊርማ ስነስርዓቱ ወቅት እንዳሉት የተደረጉት ስምምነቶች በመንግስት ልዩ ትኩረት የተሰጣቸውን ፕሮጀክቶች በመንግስትና የግል አጋርነት ማከናወን የሚያስችሉ ናቸው።

በቀጣይም ሀገራዊ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን በግልና የመንግስት አጋርነት የመፈጸም ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
የተደረጉት ስምምነቶች የሀገር ውስጥ ባለሀብቶችን በማበረታታት ትልቅ ፋይዳ እንዳላቸው በመጠቆም ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ አሳስበዋል።
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
Aug 28, 2026
መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...
Aug 18, 2026
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...
Aug 10, 2026
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026