
አሶሳ፤ ሰኔ 29/2017(ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያግዙ የመስኖ መሰረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን ገለጹ።
ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ ኡራ ወረዳ በ74 ሚሊየን ብር የተገነባ የመስኖ መሰረተ ልማት ስራ አስጀመርዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደተናገሩት መንግስት የግብርናውን ዘርፍ ለማሻሻል እና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል።
በዚህም አርሶ አደሩ ከመደበኛ የግብርና ስራው በተጨማሪ በመስኖ ልማት ተጠቃሚ እንዲሆንና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የመስኖ መሰረተ ልማት ግንባታዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል።
አርሶ አደሩ የመስኖ መሰረተ ልማትን ተጠቅሞ በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋጥ እንዳለበት ጠቁመው እየተገባደደ ባለው በጀት ዓመት ብቻ በክልሉ 11 የመስኖ ፕሮጀክቶች መጠናቀቃቸውን ገልጸዋል።

የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ ባበክር ኸሊፋ በበኩላቸው ዛሬ ለአገልግሎት የበቃው የፀንፀሎ መስኖ ፕሮጀክት በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ መጠናቀቁን ተናግረዋል።
ፕሮጀክቱ የአካባቢውን አርሶ አደር ከባህላዊ የመስኖ ስራ በማላቀቅ የመስኖ ስራውን በስፋት ለማከናወን ያግዘዋል ብለዋል።

የፀንፀሎ ቀበሌ የመስኖ ፕሮጀክት በአካባቢው የሚገኙ ሶስት ቀበሌዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግና ከ800 በላይ ነዋሪዎች በመስኖ ልማት ተሳታፊ እንደሚሆኑ ገልጸዋል።

በመስኖ ፕሮጀክቱ ምረቃ መርሃግብሩ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና የአካባቢው ማህበረሰብ ክፍሎች የተገኙ ሲሆን በመስኖ ፕሮጀክቱ አካባቢም የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተክለዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026