
አሶሳ፤ ሰኔ 29/2017(ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያግዙ የመስኖ መሰረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን ገለጹ።
ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ ኡራ ወረዳ በ74 ሚሊየን ብር የተገነባ የመስኖ መሰረተ ልማት ስራ አስጀመርዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደተናገሩት መንግስት የግብርናውን ዘርፍ ለማሻሻል እና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል።
በዚህም አርሶ አደሩ ከመደበኛ የግብርና ስራው በተጨማሪ በመስኖ ልማት ተጠቃሚ እንዲሆንና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የመስኖ መሰረተ ልማት ግንባታዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል።
አርሶ አደሩ የመስኖ መሰረተ ልማትን ተጠቅሞ በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋጥ እንዳለበት ጠቁመው እየተገባደደ ባለው በጀት ዓመት ብቻ በክልሉ 11 የመስኖ ፕሮጀክቶች መጠናቀቃቸውን ገልጸዋል።

የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ ባበክር ኸሊፋ በበኩላቸው ዛሬ ለአገልግሎት የበቃው የፀንፀሎ መስኖ ፕሮጀክት በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ መጠናቀቁን ተናግረዋል።
ፕሮጀክቱ የአካባቢውን አርሶ አደር ከባህላዊ የመስኖ ስራ በማላቀቅ የመስኖ ስራውን በስፋት ለማከናወን ያግዘዋል ብለዋል።

የፀንፀሎ ቀበሌ የመስኖ ፕሮጀክት በአካባቢው የሚገኙ ሶስት ቀበሌዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግና ከ800 በላይ ነዋሪዎች በመስኖ ልማት ተሳታፊ እንደሚሆኑ ገልጸዋል።

በመስኖ ፕሮጀክቱ ምረቃ መርሃግብሩ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና የአካባቢው ማህበረሰብ ክፍሎች የተገኙ ሲሆን በመስኖ ፕሮጀክቱ አካባቢም የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተክለዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025