
አሶሳ፤ ሰኔ 29/2017(ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያግዙ የመስኖ መሰረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን ገለጹ።
ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ ኡራ ወረዳ በ74 ሚሊየን ብር የተገነባ የመስኖ መሰረተ ልማት ስራ አስጀመርዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደተናገሩት መንግስት የግብርናውን ዘርፍ ለማሻሻል እና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል።
በዚህም አርሶ አደሩ ከመደበኛ የግብርና ስራው በተጨማሪ በመስኖ ልማት ተጠቃሚ እንዲሆንና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የመስኖ መሰረተ ልማት ግንባታዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል።
አርሶ አደሩ የመስኖ መሰረተ ልማትን ተጠቅሞ በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋጥ እንዳለበት ጠቁመው እየተገባደደ ባለው በጀት ዓመት ብቻ በክልሉ 11 የመስኖ ፕሮጀክቶች መጠናቀቃቸውን ገልጸዋል።

የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ ባበክር ኸሊፋ በበኩላቸው ዛሬ ለአገልግሎት የበቃው የፀንፀሎ መስኖ ፕሮጀክት በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ መጠናቀቁን ተናግረዋል።
ፕሮጀክቱ የአካባቢውን አርሶ አደር ከባህላዊ የመስኖ ስራ በማላቀቅ የመስኖ ስራውን በስፋት ለማከናወን ያግዘዋል ብለዋል።

የፀንፀሎ ቀበሌ የመስኖ ፕሮጀክት በአካባቢው የሚገኙ ሶስት ቀበሌዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግና ከ800 በላይ ነዋሪዎች በመስኖ ልማት ተሳታፊ እንደሚሆኑ ገልጸዋል።

በመስኖ ፕሮጀክቱ ምረቃ መርሃግብሩ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና የአካባቢው ማህበረሰብ ክፍሎች የተገኙ ሲሆን በመስኖ ፕሮጀክቱ አካባቢም የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተክለዋል።
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
Aug 28, 2026
መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...
Aug 18, 2026
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...
Aug 10, 2026
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026