
ሰኔ 30/2017 (ኢዜአ) ፡-የኦሮሚያ ክልልን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ በጥናትና ምርምር በመደገፍ ዘርፉን የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ቢሮ አስታወቀ።
ቢሮው በኢንቨስትመንት ዙሪያ የጀመረውን ስራ የበለጠ ስኬታማ ለማድረግ ከኦሮሚያ ስቴት ዩኒቨርሲቲ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል።

የኦሮሚያ ክልል ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ አቶ አህመድ ኢድሪስ በስምምነቱ ወቅት እንደተናገሩት በጥናት ላይ የተመሰረተ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ የኢኮኖሚ እድገትን ለማፋጠን ከፍተኛ ሚና ይጫወታል።
የክልሉ መንግስት የኢንቨስትመንት ዘርፉን በተሻለ መልኩ በመምራት ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግ የተለያዩ ጥረቶች እየተደረጉ መሆኑንም ገልጸዋል።
የኦሮሚያ ስቴት ዩኒቨርሲቲ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን መፍታት የሚያስችሉ የምርምር ስራዎችን በማካሄድ ሰፊ ልምድ ያለው መሆኑን ጠቅሰው ስምምነቱም ለኢንቨስትመንት ዘርፉ ውጤታማነት ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል።
ዛሬ የተደረሰው ስምምነትም የአመራሩን የማስፈፀም አቅም ለማጠናከር የሚያግዙ ስራዎችን ለመስራት፣ የፖሊሲ ቀረጻና የገበያ ትንተናን ለማከናወን ይረዳል ብለዋል።
በተለይም በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ ለማድረግ የሚያስችሉ የጥናትና ምርምር ስራዎች በጋራ የሚከናወኑ መሆኑንም ገልጸዋል።

በተጨማሪም ስምምነቱ የክልሉን ኢንዱስትሪዎች ተወዳዳሪነት ለማሳደግ፣ ኢንዱስትሪዎች ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ያላቸውን ግንኙነት ለማጠናከር እና የገበያ ትስስር ማጠናከር የሚያስችሉ የጥናትና ምርምር ስራዎች ይከናወናሉ ብለዋል።
በስምምነቱም የክልሉን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ለማስተዋወቅና የክልሉን ለኢንቨስትመንት ምቹነት ለአለም ለማሳየት በጋራ እንደሚሰራም ተናግረዋል።
በኦሮሚያ ስቴት ዩኒቨርስቲ የምርምር፣ የማማከርና የስልጠና ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ኮከብ ደመቀ (ዶ/ር) እንዳሉት በጥናትና በምርምር ለኢንቨስትመንት እድገትና ውጤታማነት ትልቅ ሚና ይጫወታል።
ዩኒቨርሲቲው ያለውን ሰፊ ልምድ ተጠቅሞ የክልሉን የኢንቨስትመንትና የኢንዱስትሪ ዘርፍ ውጤታማ የሚያደርግ ጥናትና ምርምር ስራዎች ይከናወናሉ ብለዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025