
ሰኔ 30/2017 (ኢዜአ) ፡-የኦሮሚያ ክልልን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ በጥናትና ምርምር በመደገፍ ዘርፉን የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ቢሮ አስታወቀ።
ቢሮው በኢንቨስትመንት ዙሪያ የጀመረውን ስራ የበለጠ ስኬታማ ለማድረግ ከኦሮሚያ ስቴት ዩኒቨርሲቲ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል።

የኦሮሚያ ክልል ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ አቶ አህመድ ኢድሪስ በስምምነቱ ወቅት እንደተናገሩት በጥናት ላይ የተመሰረተ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ የኢኮኖሚ እድገትን ለማፋጠን ከፍተኛ ሚና ይጫወታል።
የክልሉ መንግስት የኢንቨስትመንት ዘርፉን በተሻለ መልኩ በመምራት ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግ የተለያዩ ጥረቶች እየተደረጉ መሆኑንም ገልጸዋል።
የኦሮሚያ ስቴት ዩኒቨርሲቲ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን መፍታት የሚያስችሉ የምርምር ስራዎችን በማካሄድ ሰፊ ልምድ ያለው መሆኑን ጠቅሰው ስምምነቱም ለኢንቨስትመንት ዘርፉ ውጤታማነት ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል።
ዛሬ የተደረሰው ስምምነትም የአመራሩን የማስፈፀም አቅም ለማጠናከር የሚያግዙ ስራዎችን ለመስራት፣ የፖሊሲ ቀረጻና የገበያ ትንተናን ለማከናወን ይረዳል ብለዋል።
በተለይም በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ ለማድረግ የሚያስችሉ የጥናትና ምርምር ስራዎች በጋራ የሚከናወኑ መሆኑንም ገልጸዋል።

በተጨማሪም ስምምነቱ የክልሉን ኢንዱስትሪዎች ተወዳዳሪነት ለማሳደግ፣ ኢንዱስትሪዎች ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ያላቸውን ግንኙነት ለማጠናከር እና የገበያ ትስስር ማጠናከር የሚያስችሉ የጥናትና ምርምር ስራዎች ይከናወናሉ ብለዋል።
በስምምነቱም የክልሉን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ለማስተዋወቅና የክልሉን ለኢንቨስትመንት ምቹነት ለአለም ለማሳየት በጋራ እንደሚሰራም ተናግረዋል።
በኦሮሚያ ስቴት ዩኒቨርስቲ የምርምር፣ የማማከርና የስልጠና ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ኮከብ ደመቀ (ዶ/ር) እንዳሉት በጥናትና በምርምር ለኢንቨስትመንት እድገትና ውጤታማነት ትልቅ ሚና ይጫወታል።
ዩኒቨርሲቲው ያለውን ሰፊ ልምድ ተጠቅሞ የክልሉን የኢንቨስትመንትና የኢንዱስትሪ ዘርፍ ውጤታማ የሚያደርግ ጥናትና ምርምር ስራዎች ይከናወናሉ ብለዋል።
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
Aug 28, 2026
መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...
Aug 18, 2026
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...
Aug 10, 2026
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026