
ሀዋሳ፤ ሐምሌ 2/2017(ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ የሀዋሳ ከተማን ልማት በማፋጠን ለህዝብ ጥያቄ ምላሽ መስጠት ላይ ትኩረትመደረጉን የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ መኩሪያ መርሻዬ ገለጹ።
ከንቲባው የበጀት ዓመቱን የልማትና መልካም አስተዳደር ሥራዎች አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል።
ከንቲባው በመግለጫቸው የከተማው ህብረተሰብ የልማት ጥያቄ ከሆኑት መካከል በተለይም የመንገድ፣ የውሃ፣ መብራትና ሌሎች ስራዎችን ደረጃ በደረጃ ምላሽ ለመስጠት መሰራቱን ጠቅሰዋል።
በከተማዋ ለተከናወነው ከ207 ኪሎ ሜትር በላይ የመንገድ ከፈታ ስራ ህብረተሰቡ ቋሚ ንብረቶቹን በማንሳቱ ለስራው መቀላጠፍ አጋዥ እንደነበርም ገልጸዋል።
በከተማዋ ውበትና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ላይ ጉልህ ሚና ያለው የ2 ነጥብ 2 ኪሎ ሜትር የመጀመሪያው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ሥራም ተጠናቆ ለአገልግሎት መብቃቱን አንስተዋል፡፡
ስራውን በማስቀጠል 5 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሁለተኛው ምዕራፍ ኮሪደር ልማትም 60 በመቶው መጠናቀቁን አክለዋል።
የከተማዋን የንፁህ መጠጥ ውሃ እጥረት ለመፍታት በ260 ሚሊዮን ብር የፋራ-ሂጣታ የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
ከ100ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርገው ይህ የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት አፈጻጸምም 75 በመቶ መድረሱን አብራርተዋል፡፡
በሥራ ዕድል ፈጠራ፣ በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በአገልግሎትና ሌሎች ዘርፎችም ለ18ሺህ 341 ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል ብለዋል፡፡
ለቱሪዝም ዘርፉ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው በበጀት ዓመቱ ወደ ከተማዋ ከመጡ የውጭና የሀገር ውስጥ ጎብኚዎች 861 ሚሊዮን ብር ገቢ መገኘቱንም ጠቅሰዋል፡፡
ከተማ አስተዳደሩ የህብረተሰቡን የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ የገቢ አቅምን ማሳደግ ላይ ትኩረት በመስጠቱ 4 ቢሊዮን 535 ሚሊዮን ብር መሰብሰብ እንደተቻለ አስረድተዋል፡፡
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026