የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የኢትዮጵያ የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ ባለፉት ሁለት ዓመታት አበረታች ተግባር አከናውኗል

Jul 11, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 3/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ ባለፉት ሁለት ዓመታት አበረታች ተግባር ማከናወኑን የብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ እና የኢትዮጵያ ተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ የቦርድ ሊቀ መንበር ሰለሞን ደስታ ገለጹ።

የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ ግንዛቤን ለማሳደግ ያለመ ወርክሾፕ ተካሂዷል።

የብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ አቶ ሰለሞን ደስታ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት የሀገሪቱ የፋይናንስ ስርዓት ጤናማ፣ ለአደጋ ያልተጋለጠና የተረጋጋ እንዲሆን ፈንዱ የበኩሉን ሚና ይጫወታል፡፡


ለገንዘብ አስቀማጮች ተገቢውን ጥበቃ በማድረግ ለፋይናንስ ሥርዓቱ መረጋጋት የላቀ አስተዋጽዖ ከማበርከት ባለፈ የሀገሪቱን የፋይናንስ ዘርፍ ለማረጋጋት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ገልጸዋል።

ፈንዱ ከተመሠረተበት ጊዜ አንስቶ በርካታ ሥራዎችን በማቀድ የተጣለበትን ኃላፊነት በተሟላ እና በሚፈለገው ደረጃ እየተወጣ ይገኛል ነው ያሉት።

ባለፉት ሁለት ዓመታት አረቦን በመሰብሰብ ረገድ አበረታች ስራ መስራቱንም ተናግረዋል።

የአባል ተቋማት ቁጥር 86 መድረሱን ተናግረው 32 ባንኮችና እና 54 ማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት አባል መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

ገንዘብ አስቀማጮች እና ባለድርሻ አካላት ስለፈንዱ በቂ ግንዛቤና ዕውቀት እንዲኖራቸው መሰል መድረኮችን በማጠናከር ግንዘቤን ማስፋት እንደሚገባም ነው ያስታወቁት።

የኢትዮጵያ የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ደሳለኝ አምባው (ዶ/ር) በበኩላቸው ፈንዱ በአጭር ጊዜ ውስጥ በርካታ ሥራዎችን በማከናወን አመርቂ ውጤቶችን ማስመዝገቡን ተናግረዋል።


ፈንዱን በማደራጀት እና ለሥራ የሚያስፈልጉ የሰው ኃይል እና ሌሎች ግብዓቶችን በማሟላት ረገድ አበረታች ሥራ መስራቱን ጠቅሰዋል።

በዚህም ፈንዱ ባለፉት ሁለት ዓመታት ከአባል የፋይናንስ ተቋማት 13 ነጥብ 84 ቢሊዮን ብር መነሻ እና ዓመታዊ አረቦን መሰብሰቡን ገልጸው፥ የመንግሥት ግምጃ ቤት ሰነድ ላይ ኢንቨስት በማድረግም ትርፍ እያስመዘገበ መሆኑን ጠቁመዋል።

ፈንዱ በቀጣይ የአረቦን የመሰብሰብ አቅሙን እንደሚያሳድግ፣ አገልግሎቱን በቴክኖሎጂ እንደሚያዘመን እና ግንዛቤ የመፍጠር ሥራን እንደሚያጠናክር ተናግረዋል።

ፈንዱ በንግድ ባንኮችም ሆነ በአነስተኛ ፋይናንስ ተቋማት ገንዘብ ለሚቆጥበው ወይም ለሚያስቀምጠው ማኅብረሰብ ዋስትና የሚሰጥ ሲሆን፣ በባንኮች ላይ ወይም ማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት ላይ አደጋ ቢያጋጥም፣ አስቀማጮች ካሳ የሚያገኙበት ስርዓት ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026