የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የአፍሪካ ህብረት አባል አገራት የነጻ ንግድ ቀጣና ቁልፍ የማስተግበሪያ ደንቦች አፅድቀው ወደ ስራ እንዲያስገቡ ጥሪ አቀረበ

Jul 11, 2025

IDOPRESS


አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 3/2017(ኢዜአ)፦የአፍሪካ አባል ህብረት አገራት የአህጉራዊውን ነጻ ንግድ ቀጣና ቁልፍ የማስፈጸሚያ የህግ ማዕቀፎችን በማጽደቅ ወደ ስራ እንዲያስገቡ አሳሰበ።

47ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ዛሬ በኢኳቶሪያል ጊኒ ማላቦ ተጀምሯል።

ስብሰባው “ የማካካሻ ፍትህ ለአፍሪካውያንና ለዘርዓ-አፍሪካውያን” በሚል ሀሳብ እየተከናወነ ይገኛል።

የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ የምክር ቤቱ ዋንኛ የውይይት አጀንዳ የህብረቱ የእ.አ.አ 2026 በጀት መሆኑን ገልጸዋል።

ከዚህ አንጻር የህብረቱ ፕሮግራም በጀት በራስ አቅም የመሸፈን ስራ መጠነኛ ለውጥ ቢያሳይም ብዙ ስራዎች እንደሚቀሩ ተናግረዋል።

ይሁንና እ.አ.አ በ2016 የህብረቱ አባል ሀገራት ወደ አፍሪካ የሚገቡ የተመረጡ እቃዎች ላይ የ0 ነጥብ 2 በመቶ ቀረጥ በመጣል የአህጉራዊውን ተቋም የፋይናንስ አቅም ማጠናከር የሚያስችለውን ውሳኔ ሀሳብ (kigali decision) ቢያፀድቁም በሚፈለገው ደረጃ እየተገበሩት እንዳልሆነ አመልክተዋል።

ከህብረቱ አባል ሀገራት መካከል 17ቱ ብቻ ስምምነቱን እየተገበሩ ነው ያሉት ሊቀ መንበሩ የህብረቱን የፋይናንስ ነጻነት ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት እንዲሰሩ አሳስበዋል።

ሱዳን፣ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ጎንጎ፣ ሶማሊያ እና ሳሄል ቀጣናን ጨምሮ በአህጉሪቷ ያሉ የፖለቲካ አለመረጋጋቶች፣ የሰብዓዊ ቀውሶች እና የደህንነት ችግር አሁን የአፍሪካ ልማት አጀንዳ እንዳይሳካ መሰናክል ሆኖ ቀጥሏል ነው ያሉት ሊቀ መንበሩ።

የአፍሪካ ህብረት የድጋፍ እና የማረጋጋት ተልዕኮ (አውሶም) የሰላም አስከባሪ ኃይል ያጋጠመው የፋይናንስ እጥረት ልዩ ትኩረት እንደሚያሻው ተናግረዋል።

እነዚህ ፈተናዎች ቢኖሩም በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና በሩዋንዳ መካከል የተደረገው ስምምነት፣ የጋቦን ወደ ህገ መንግስታዊ ስርዓት መመለስ እና የጊኒ የሽግግር እቅድ ተስፋን የሚያጭሩ መልካም ለውጦች መሆናቸውን በማሳያነት ጠቅሰዋል።

የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ከቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች፣ ከህብረቱ የሰላም እና ደህነንት ምክር ቤት እንዲሁም ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ጋር ቀጣይነት ባለው መልኩ ትብብሩን በማጠናከር የሰላም ጥረቶችን መደገፉን እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

በተጨማሪም ሊቀ መንበሩ የህብረቱ አባል ሀገራት የተቋማዊ ሪፎርም ስራን እንዲያፋጥኑንና የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ማስፈጸሚያ ደንቦችን አፅድቀው ወደ ስራ በማስገባት ለቀጣናዊ ትስስር የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ ጥሪ ማቅረባቸውን ኢዜአ ከተቋሙ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

47ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብስባ እስከ ነገ ይቆያል።

ከምክር ቤቱ ስብሰባ ጎን ለጎን ሐምሌ 7 ቀን 2017 ዓ.ም የህብረቱ የ7ተኛ የመንፈቅ ዓመት የባለድርሻ አካላት የትብብር ስብሰባ ይደረጋል።


#Ethiopian_News_Agency #Ethiopia #ኢትዮጵያ #ኢዜአ

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026