
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 3/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቪየትናም ዋና ከተማ ሃኖይ አዲስ የመንገደኞች በረራጀምሯል።
በማስጀመሪያ መርሀግብሩ የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ደንጌ ቦሩ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው የአየር መንገዱ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች የቪየትናም የንግድ ተቋማት ተወካዮች ታድመዋል።
አየር መንገዱ በሳምንት አራት ጊዜ የመንገደኞች በረራ የሚያደርግ መሆኑ ተገልጿል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው በዚሁ ወቅት እንዳሉት በረራው የሀገራቱን ግንኙነት የሚያጎለብት ነው።
ይህ አዲስ መስመር በኢትዮጵያ እና ቪየትናም መካከል ያለውን የንግድ፣ ቱሪዝም እና የባህል ልውውጥ የሚያሳድግ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
እንዲሁም በአፍሪካ እና በደቡብ ምሥራቅ እስያ መካከል ቀጥተኛ ትስስር እንዲኖር በማድረግ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ስትራቴጂካዊ መስፋፋት በማጠናከር ዓለም አቀፍ ግንኙነትን የሚያጎለብት መሆኑን ተናግረዋል።
የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ደንጌ ቦሩ፥ አየር መንገዱ የስኬት ማሳያ የሆነ ተቋም መሆኑን ገልጸዋል።
አየር መንገዱ እንደ ሀገር የተያዙ ኢኮኖሚያዊ እቅዶች እንዲሳኩ የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን አንስተዋል።
በረራው የሀገራቱን ግንኙነት በጉልህ የሚያሳድግ መሆኑን ተናግረዋል።
በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የመካከለኛው ምስራቅ እስያ እና ፓስፊክ ሀገራት ጉዳዮች ዳይሬክተር ጀነራል ደዋኖ ከድር በበኩላቸው አየር መንገዱ ለዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ጉልህ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ገልጸዋል።
በሁለቱ ሀገራት መካከል የተጀመረው በረራ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጠቀሜታ እንዳለው አመላክተዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026