
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 3/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቪየትናም ዋና ከተማ ሃኖይ አዲስ የመንገደኞች በረራጀምሯል።
በማስጀመሪያ መርሀግብሩ የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ደንጌ ቦሩ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው የአየር መንገዱ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች የቪየትናም የንግድ ተቋማት ተወካዮች ታድመዋል።
አየር መንገዱ በሳምንት አራት ጊዜ የመንገደኞች በረራ የሚያደርግ መሆኑ ተገልጿል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው በዚሁ ወቅት እንዳሉት በረራው የሀገራቱን ግንኙነት የሚያጎለብት ነው።
ይህ አዲስ መስመር በኢትዮጵያ እና ቪየትናም መካከል ያለውን የንግድ፣ ቱሪዝም እና የባህል ልውውጥ የሚያሳድግ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
እንዲሁም በአፍሪካ እና በደቡብ ምሥራቅ እስያ መካከል ቀጥተኛ ትስስር እንዲኖር በማድረግ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ስትራቴጂካዊ መስፋፋት በማጠናከር ዓለም አቀፍ ግንኙነትን የሚያጎለብት መሆኑን ተናግረዋል።
የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ደንጌ ቦሩ፥ አየር መንገዱ የስኬት ማሳያ የሆነ ተቋም መሆኑን ገልጸዋል።
አየር መንገዱ እንደ ሀገር የተያዙ ኢኮኖሚያዊ እቅዶች እንዲሳኩ የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን አንስተዋል።
በረራው የሀገራቱን ግንኙነት በጉልህ የሚያሳድግ መሆኑን ተናግረዋል።
በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የመካከለኛው ምስራቅ እስያ እና ፓስፊክ ሀገራት ጉዳዮች ዳይሬክተር ጀነራል ደዋኖ ከድር በበኩላቸው አየር መንገዱ ለዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ጉልህ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ገልጸዋል።
በሁለቱ ሀገራት መካከል የተጀመረው በረራ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጠቀሜታ እንዳለው አመላክተዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025