የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ዩኒቨርሲቲው ዘመናዊ የሠራዊት ግንባታን በቴክኖሎጂ የሚያጠናክሩ ብቁ ሙያተኞች እያፈራ ነው - ሚኒስትር አይሻ መሐመድ(ኢ/ር)

Jul 14, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ዘመናዊ የሰራዊት ግንባታን በቴክኖሎጂ የሚያጠናክሩ ብቃትና ሥነ-ምግባር ያላቸው ሙያተኞች እያፈራ እንደሚገኝ የመከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሐመድ(ኢ/ር) ገለጹ።

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ በምህንድስና፣ በጤና ሳይንስ፣ በቢዝነስ እና በኃብት አስተዳደር እንዲሁም በሌሎች የትምህርት መርኃ ግብሮች በመጀመሪያ፣ በሁለተኛ እና በሶስተኛ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎችን ዛሬ አስመርቋል።


በምረቃ መርኃ ግብሩ የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሐመድ፣ የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ(ዶ/ር)፣ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ እና የዩኒቨርሲቲው ምክትል የቦርድ ሰብሳቢ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ፣ የመከላከያ ከፍተኛ መኮንኖች፣ የተለያዩ ሀገራት ወታደራዊ አታሼዎችና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።

በምረቃ መርኃ ግብሩ ላይ የተገኙት የመከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሐመድ(ኢ/ር) ለተመራቂዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የዛሬው ተመራቂዎች ኢትዮጵያ በየዘመኑ ጀግኖችን የምታፈራ ሀገር ለመሆኗ ትልቅ ማሣያ ናችሁ ብለዋል።

የመከላከያ ዩኒቨርሲቲ የሰለጠነ የሠራዊት አባላትንና ሲቪል አመራር በማፍራት ላይ እንደሚገኝ ጠቁመው በዚህም በእውቀት፣ በዓላማና በሙያዊ ልህቀት የታነጹ ሙያተኞችን እያፈራ ይገኛል ብለዋል።

የሠራዊቱን የወታደራዊ ቴክኖሎጂ ብቃት ለማላቅ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው በተለይም ዘመናዊ የሰራዊት ግንባታን በቴክኖሎጂ ማገዝ የሚችሉ ብቁና ሥነ-ምግባር ያላቸውን ሙያተኞች እያፈራ መሆኑን ተናግረዋል።

በሌላ መልኩም በምርምርና በማህበረሰብ አገልግሎት በርካታ ስራዎችን እየሰራ መሆኑንም ሚኒስትሯ ገልጸዋል።

ዩኒቨርሲቲው ለሀገርና ለመጪው ትውልድ የሚሻገር ስራ መሥራቱን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አሳስበዋል።

ተመራቂዎች በታማኝነት፣ በቅንነትና በስነምግባር ሀገራቸውን ማገልገል እንዳለባቸው በአፅንኦት ተናግረዋል።

በምርቃት መርኃ ግብሩ ላይ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተመራቂዎች ሽልማት ተበርክቷል።

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ በ2025 ከአፍሪካ አምስት ምርጥ የመከላከያ ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ የመሆን ራዕይ ሰንቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026