የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የኑሮ ውድነትን ለማቃለል በሚደረገው ጥረት የክልሎች የምርት አቅርቦት ትብብርና ትስስር ሊጠናከር ይገባል

Jul 17, 2025

IDOPRESS

ድሬዳዋ ፤ ሐምሌ 9/2017(ኢዜአ)፦የኑሮ ውድነትን ለማቃለል በሚደረገው ጥረት የክልሎች የምርት አቅርቦት ትብብርና ትስስር ሊጠናከር ይገባል ሲሉ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንትና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ አደም ፋራህ ገለፁ።

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በመንግስት እና በፓርቲ ትብብር የተከናወኑ አበይት ተግባራትን የሚገመግም መድረክ በድሬዳዋ ተካሂዷል።

የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንትና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ አደም ፋራህ፤ በማጠቃለያ ንግግራቸው በቀጣይ ትኩረት በሚሹ ጉዳዮችና መሰራት ስላለባቸው ቀጣይ አቅጣጫዎች ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ሀገርንና ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ ዘርፈ ብዙ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተው በተለይም የኑሮ ውድነትን በማቃለል ረገድ በቀጣይ ብዙ ስራዎች ይጠበቃሉ ብለዋል።

በዚህ ረገድ ጅምሮቹ ጥሩ መሆናቸውን አንስተው እንደየ ክልሎቹ ነባራዊ ሁኔታ ምርቶችን በመለየትና አቅርቦትና ምርታማነትን በማሳለጥ በቀጣይም ብዙ መስራት ይገባል ብለዋል።

በምርት አቅርቦት ረገድ የክልሎች ትብብርና ጥብቅ ትስስር አስፈላጊ በመሆኑ በቀጣይ በልዩ ትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።


የቅዳሜ እና እሁድ ግብይቶችን ጨምሮ ለገበያ ማረጋጋትና የኑሮ ውድነትን ለማቃለል በየደረጃው ያሉ አመራሮችና የሚመለከታቸው አካላት ተጨማሪ ስራ የሚጠይቅ መሆኑን አንስተው የኮንትሮባንድ ንግድንና የገበያ አሻጥሮችን በጥብቅ በመከታተል ችግሮቹን በዘላቂነት ለመፍታትም በቅንጅት መስራት ይገባልም ብለዋል።

የድሃ ተኮር ፕሮግራሞችን አጠናክሮ መቀጠል፣ የአመጋገብ ባህል እንዲሻሻል መጣርና የምርት አማራጮችን ማስፋትም እንዲሁ።

ከስራ እድል ፈጠራ አንፃር መልካም ጅምሮች መኖራቸውን የጠቀሱት አቶ አደም የሚስተዋሉ ችግሮችን በጥልቀት በማየት በዘላቂነት መፍታት እንደሚገባ አሳስበዋል።

በተለይም የብድር ሁኔታን የማመቻቸት፣ የስልጠና እድሎችን የማስፋትና የሰዎች የአስተሳሰብ በመለወጥ ረገድ እንዲሁም የስራ እና የመሸጫ ቦታዎችን በአግባቡ ጥቅም ላይ እንዲውሉ አመራሩ በትኩረት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

ከተረጅነት ለመውጣት በሚደረገው ጥረት ከቤተሰብ እቅድ ጀምሮ የድጋፍና ክትትል ስራን በማጠናከር ከሌማት ትሩፋትና ሌሎች የምግብ ሉአላዊነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ኢኒሸቲቮች ትግበራ ጋር ጥብቅ ቁርኝት እንዲፈጠር መስራት ያስፈልጋል ብለዋል አቶ አደም።

የሰብአዊ ድጋፍን በራስ አቅም ምላሽ ለመስጠትና ዘላቂ መፍትሄ ለመሻትም የመጠባበቂያ ክምችትን ማሳደግና ጠንካራ የአሰራር ስርአት መዘርጋት አስፈላጊ መሆኑንም አንስተዋል።

ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎችን በጥንቃቄ በመለየት ለፈጣን ምላሽ፣ በቂና የተሟላ ዝግጅት አስፈላጊ መሆኑንም አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026