የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የኑሮ ውድነትን ለማቃለል በሚደረገው ጥረት የክልሎች የምርት አቅርቦት ትብብርና ትስስር ሊጠናከር ይገባል

Jul 17, 2025

IDOPRESS

ድሬዳዋ ፤ ሐምሌ 9/2017(ኢዜአ)፦የኑሮ ውድነትን ለማቃለል በሚደረገው ጥረት የክልሎች የምርት አቅርቦት ትብብርና ትስስር ሊጠናከር ይገባል ሲሉ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንትና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ አደም ፋራህ ገለፁ።

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በመንግስት እና በፓርቲ ትብብር የተከናወኑ አበይት ተግባራትን የሚገመግም መድረክ በድሬዳዋ ተካሂዷል።

የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንትና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ አደም ፋራህ፤ በማጠቃለያ ንግግራቸው በቀጣይ ትኩረት በሚሹ ጉዳዮችና መሰራት ስላለባቸው ቀጣይ አቅጣጫዎች ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ሀገርንና ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ ዘርፈ ብዙ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተው በተለይም የኑሮ ውድነትን በማቃለል ረገድ በቀጣይ ብዙ ስራዎች ይጠበቃሉ ብለዋል።

በዚህ ረገድ ጅምሮቹ ጥሩ መሆናቸውን አንስተው እንደየ ክልሎቹ ነባራዊ ሁኔታ ምርቶችን በመለየትና አቅርቦትና ምርታማነትን በማሳለጥ በቀጣይም ብዙ መስራት ይገባል ብለዋል።

በምርት አቅርቦት ረገድ የክልሎች ትብብርና ጥብቅ ትስስር አስፈላጊ በመሆኑ በቀጣይ በልዩ ትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።


የቅዳሜ እና እሁድ ግብይቶችን ጨምሮ ለገበያ ማረጋጋትና የኑሮ ውድነትን ለማቃለል በየደረጃው ያሉ አመራሮችና የሚመለከታቸው አካላት ተጨማሪ ስራ የሚጠይቅ መሆኑን አንስተው የኮንትሮባንድ ንግድንና የገበያ አሻጥሮችን በጥብቅ በመከታተል ችግሮቹን በዘላቂነት ለመፍታትም በቅንጅት መስራት ይገባልም ብለዋል።

የድሃ ተኮር ፕሮግራሞችን አጠናክሮ መቀጠል፣ የአመጋገብ ባህል እንዲሻሻል መጣርና የምርት አማራጮችን ማስፋትም እንዲሁ።

ከስራ እድል ፈጠራ አንፃር መልካም ጅምሮች መኖራቸውን የጠቀሱት አቶ አደም የሚስተዋሉ ችግሮችን በጥልቀት በማየት በዘላቂነት መፍታት እንደሚገባ አሳስበዋል።

በተለይም የብድር ሁኔታን የማመቻቸት፣ የስልጠና እድሎችን የማስፋትና የሰዎች የአስተሳሰብ በመለወጥ ረገድ እንዲሁም የስራ እና የመሸጫ ቦታዎችን በአግባቡ ጥቅም ላይ እንዲውሉ አመራሩ በትኩረት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

ከተረጅነት ለመውጣት በሚደረገው ጥረት ከቤተሰብ እቅድ ጀምሮ የድጋፍና ክትትል ስራን በማጠናከር ከሌማት ትሩፋትና ሌሎች የምግብ ሉአላዊነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ኢኒሸቲቮች ትግበራ ጋር ጥብቅ ቁርኝት እንዲፈጠር መስራት ያስፈልጋል ብለዋል አቶ አደም።

የሰብአዊ ድጋፍን በራስ አቅም ምላሽ ለመስጠትና ዘላቂ መፍትሄ ለመሻትም የመጠባበቂያ ክምችትን ማሳደግና ጠንካራ የአሰራር ስርአት መዘርጋት አስፈላጊ መሆኑንም አንስተዋል።

ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎችን በጥንቃቄ በመለየት ለፈጣን ምላሽ፣ በቂና የተሟላ ዝግጅት አስፈላጊ መሆኑንም አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026