
ታርጫ፣ ሐምሌ 16/2017 (ኢዜአ):-በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በተለያዩ ዘርፎች የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማስቀጠል የክትትልና ድጋፍ ተግባራችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉ የክልሉ ምክር ቤት አባላት ተናገሩ፡፡
የክልሉ ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 8ኛ መደበኛ ጉባኤውን በታርጫ ከተማ አካሄዷል፡፡

አባላቱ በሚያደርጉት ቅኝትና ክትትል በተጠናቀቀው በክልሉ በጀት ዓመቱ በኢኮኖሚ፣ ማህበራዊና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች የተሻለ አፈጻጸም መኖሩን መመልከታቸውን ገልጸው ይህም በቀጣይ በተቀናጀ አግባብ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።
አስተያየታቸውን የሰጡ የምክር ቤት አባላቱ እንዳሉት፤ በክልሉ በተለያዩ ዘርፎች የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማስቀጠል የክትትልና ድጋፍ ተግባራችንን አጠናክረን እንቀጥላለን።
ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል ወይዘሮ እንግዳወርቅ ዶኖቾ፣ እንዳሉት በክልሉ በበጀት ዓመቱ የህዝብን ጥያቄ መሰረት ያደረጉ የልማት እንቅስቃሴዎች መከናወናቸውን ምልከታ ባደረጉበት ወቅት ማስተዋላቸውን ተናግረዋል።
ከመሰረተ ልማት አኳያ በተደጋጋሚ በምክር ቤቱ ሲነሱ የነበሩ ተጀምረው ያልተጠናቀቁና የህብረተሰቡ የቅሬታ ምንጭ ሆነው የቆዩ ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ የተወሰደው የተቀናጀ እርምጃ ውጤታማ መሆኑንም እንዲሁ።

ህብረተሰቡንና ሌሎች ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ የተከናወኑ የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራት ላይ የተሰሩ ስራዎች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ያነሱት ደግሞ ሌላኛው የምክር ቤቱ አባል መስፍን ወዳጆ (ዶ/ር) ናቸው።
የምክር ቤቱ አባል አቶ ተረፈ ሀብተማሪያም በበኩላቸው በክልሉ የሚከናወኑ የልማት ስራዎች የህዝብን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ እንዲሆኑ ምክር ቤቱ የሚጠበቅበትን ለመወጣት እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል።

የትምህርት ቤቶችን ደረጃ በማሻሻልና በጤናው ረገድ ቅድመ መከላከል ላይ የተከናወኑ ተግባራት ውጤት የታየባቸው መሆኑን ገልጸው የበለጠ ማጠናከር ይጠበቃል ብለዋል ።
በግብርናው ዘርፍ የተመዘገበው ውጤት ቀጣይነት እንዲኖረው በቴክኖሎጂ የማስደገፍ ስራ ትኩረት ሊጠሰው እንደሚገባ የገለፁት አባላቱ ፣ የስራ ዕድል ፈጠራና ትምህርት ለትውልድ ላይ የተጀመሩ ጥረቶች ሊጠናከሩ ይገባል ብለዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025