የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በክልሉ በተለያዩ ዘርፎች የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማስቀጠል የክትትልና ድጋፍ ተግባራችንን አጠናክረን እንቀጥላለን-የምክር ቤት አባላት

Jul 24, 2025

IDOPRESS

ታርጫ፣ ሐምሌ 16/2017 (ኢዜአ):-በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በተለያዩ ዘርፎች የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማስቀጠል የክትትልና ድጋፍ ተግባራችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉ የክልሉ ምክር ቤት አባላት ተናገሩ፡፡

የክልሉ ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 8ኛ መደበኛ ጉባኤውን በታርጫ ከተማ አካሄዷል፡፡


አባላቱ በሚያደርጉት ቅኝትና ክትትል በተጠናቀቀው በክልሉ በጀት ዓመቱ በኢኮኖሚ፣ ማህበራዊና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች የተሻለ አፈጻጸም መኖሩን መመልከታቸውን ገልጸው ይህም በቀጣይ በተቀናጀ አግባብ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።

አስተያየታቸውን የሰጡ የምክር ቤት አባላቱ እንዳሉት፤ በክልሉ በተለያዩ ዘርፎች የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማስቀጠል የክትትልና ድጋፍ ተግባራችንን አጠናክረን እንቀጥላለን።

ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል ወይዘሮ እንግዳወርቅ ዶኖቾ፣ እንዳሉት በክልሉ በበጀት ዓመቱ የህዝብን ጥያቄ መሰረት ያደረጉ የልማት እንቅስቃሴዎች መከናወናቸውን ምልከታ ባደረጉበት ወቅት ማስተዋላቸውን ተናግረዋል።

ከመሰረተ ልማት አኳያ በተደጋጋሚ በምክር ቤቱ ሲነሱ የነበሩ ተጀምረው ያልተጠናቀቁና የህብረተሰቡ የቅሬታ ምንጭ ሆነው የቆዩ ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ የተወሰደው የተቀናጀ እርምጃ ውጤታማ መሆኑንም እንዲሁ።


ህብረተሰቡንና ሌሎች ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ የተከናወኑ የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራት ላይ የተሰሩ ስራዎች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ያነሱት ደግሞ ሌላኛው የምክር ቤቱ አባል መስፍን ወዳጆ (ዶ/ር) ናቸው።

የምክር ቤቱ አባል አቶ ተረፈ ሀብተማሪያም በበኩላቸው በክልሉ የሚከናወኑ የልማት ስራዎች የህዝብን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ እንዲሆኑ ምክር ቤቱ የሚጠበቅበትን ለመወጣት እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል።


የትምህርት ቤቶችን ደረጃ በማሻሻልና በጤናው ረገድ ቅድመ መከላከል ላይ የተከናወኑ ተግባራት ውጤት የታየባቸው መሆኑን ገልጸው የበለጠ ማጠናከር ይጠበቃል ብለዋል ።

በግብርናው ዘርፍ የተመዘገበው ውጤት ቀጣይነት እንዲኖረው በቴክኖሎጂ የማስደገፍ ስራ ትኩረት ሊጠሰው እንደሚገባ የገለፁት አባላቱ ፣ የስራ ዕድል ፈጠራና ትምህርት ለትውልድ ላይ የተጀመሩ ጥረቶች ሊጠናከሩ ይገባል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026