
ደብረ ማርቆስ፤ ሐምሌ 17/2017 (ኢዜአ)፡-በምስራቅ ጎጃም ዞን ሰላምን በማስፈንና ዘላቂነቱን ለማረጋገጥ የተሰራው ሥራ ለሌሎች የልማት ሥራዎች መፋጠን መደላድልን እየፈጠረ መምጣቱን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ።
በዞኑ በበጀት ዓመቱ ከ115 ሺህ በላይ ዜጎች የሥራ እድል ተጠቃሚ መሆናቸውንም አስተዳደሩ አስታውቋል።
የዞኑ አስተዳደር የተጠናቀቀው በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ በደብረ ማርቆስ ከተማ ተካሄዷል።

የዞኑ አስተዳደር አማካሪ አቶ ሙሉቀን ቢያድግልኝ በመድረኩ እንደገጹት በበጀት ዓመቱ የሰላም፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎችን በማጠናከር ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ ተሰርቷል።
በየደረጃው ሰላምን ለማስፈንና ዘላቂነቱን ለማረጋገጥ የተሰራው ሥራ ለሌሎች የልማት ሥራዎች መፋጠን መደላድልን እየፈጠረ መምጣቱን ገልጸዋል።
በዞኑ የተገኘውን ሰላም በመጠቀም በበጀት ዓመቱ ለ115 ሺህ 747 ሥራ አጥ ወገኖች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ እድል ለመፍጠር መቻሉን ተናግረዋል።
የግብርናውን ዘርፍ ምርታማነት ለማሳደግ በተሰራው ሥራም በሄክታር ከ27 ኩንታል በታች የነበረውን ወደ 35 ኩንታል ማሳደግ ተችሏል ብለዋል።
ሲቪል ሰርቫንቱ የአገልጋይነት መንፈስን በመላበስ ከአድሎና ብልሹ አሰራር በጸዳ መልኩ አገልግሎት በመስጠት መልካም አስተዳደርን ለማስፈን በተሰራው ስራ ውጤት እየተገኘ መምጣቱንም ገልጸዋል።
የዞኑ ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ የሺዋስ አንዷለም በበኩላቸው በበጀት ዓመቱ የጤና መድህን አገልግሎትን በማስፋትና በሁሉም ቀበሌዎች የጤና ኤክስቴንሽን ሠራተኞችን በማሰማራት የተገልጋዩን እርካታ ለማሳደግ መሰራቱን አመልክተዋል።
የዞኑ ስራና ስልጠና መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ አበጀ አላምረው በበኩላቸው በበጀት ዓመቱ ቅንጅታዊ አሰራርን በማዳበር በስራ እድል ፈጠራ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን አውስተዋል።
በዚህም የስራ እድል ለመፍጠር ከታቀደው ውስጥ 76 በመቶ የሚሆነውን ለማሳካት መቻሉንም ተናግረዋል።
በግምገማ መድረኩ ላይ በዞኑ የሚገኙ ተቋማት ኃላፊዎችና የተለያዩ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
Aug 28, 2026
መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...
Aug 18, 2026
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...
Aug 10, 2026
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026