
ሀዋሳ፤ሐምሌ 22/2017 (ኢዜአ)፦የሀዋሳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን በበጀት ዓመቱ ወደ ውጭ ከላካቸው ምርቶች ከ45 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ማስገኘቱን አስታወቀ።
የልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ማቲዮስ አሸናፊ ለኢዜአ እንደገለጹት፥ የሀዋሳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን ከዚህ ቀደም በጨርቃ ጨርቅ ምርቶች ላይ ትኩረት አድርጎ ሲሰራ መቆየቱን አስታውሰዋል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን መሆኑን ተከትሎ በተለያዩ ዘርፎች ለመሰማራት ፍላጎት ያላቸው ባለሀብቶች ወደልዩ ዞኑ ለመግባት ስምምነት እየፈረሙ መሆኑን ገልጸዋል።
በተለይ የምስራቅ እስያ ካምፓኒዎች በብዛት እየገቡ እንደሚገኙ ጠቁመው፣ከእነዚህም በዓለም አቀፍ ደረጃ በሶላር ምርት ዕውቅና ያላቸው እንደ ቶዮ ሶላር፣ ካናዳ ሶላር እና ኦርጂን ሶላር የመሳሰሉ ካምፓኒዎች ፋብሪካቸውን ተክለው ወደምርት ሂደት መግባታቸውን ተናግረዋል፡፡
ይህም ከፍተኛ የሆነ የቴክኖሎጂ ዕውቀት ሽግግር፣የሥራ ዕድል ፈጠራ እንዲሁም የወጪ ምርት መጠን እንዲጨምር እና ገቢም እንዲያድግ ማድረጉን ተናግረዋል።
የሀዋሳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን በበጀት ዓመቱ ወደ ተለያዩ ሀገራት ከላካቸው ምርቶች ከ45 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱንም አቶ ማቲዮስ አንስተዋል፡፡
ገቢው የተገኘው ወደ አውሮፓ፣ሰሜን አሜርካ፣ እስያና አፍርካ ውስጥ በሚገኙ 14 የገበያ መዳረሻዎች ከተላኩ ምርቶች መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በሀዋሳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ከዚህ ቀደም ሥራ ላይ ከነበሩ ኩባንያዎች በተጨማሪ የተለያዩ ኩባንያዎች ስምምነት ፈርመው ወደ ምርት ሂደት መግባታቸው ተገልጿል፡፡
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025