
ሀዋሳ፤ሐምሌ 22/2017 (ኢዜአ)፦የሀዋሳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን በበጀት ዓመቱ ወደ ውጭ ከላካቸው ምርቶች ከ45 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ማስገኘቱን አስታወቀ።
የልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ማቲዮስ አሸናፊ ለኢዜአ እንደገለጹት፥ የሀዋሳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን ከዚህ ቀደም በጨርቃ ጨርቅ ምርቶች ላይ ትኩረት አድርጎ ሲሰራ መቆየቱን አስታውሰዋል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን መሆኑን ተከትሎ በተለያዩ ዘርፎች ለመሰማራት ፍላጎት ያላቸው ባለሀብቶች ወደልዩ ዞኑ ለመግባት ስምምነት እየፈረሙ መሆኑን ገልጸዋል።
በተለይ የምስራቅ እስያ ካምፓኒዎች በብዛት እየገቡ እንደሚገኙ ጠቁመው፣ከእነዚህም በዓለም አቀፍ ደረጃ በሶላር ምርት ዕውቅና ያላቸው እንደ ቶዮ ሶላር፣ ካናዳ ሶላር እና ኦርጂን ሶላር የመሳሰሉ ካምፓኒዎች ፋብሪካቸውን ተክለው ወደምርት ሂደት መግባታቸውን ተናግረዋል፡፡
ይህም ከፍተኛ የሆነ የቴክኖሎጂ ዕውቀት ሽግግር፣የሥራ ዕድል ፈጠራ እንዲሁም የወጪ ምርት መጠን እንዲጨምር እና ገቢም እንዲያድግ ማድረጉን ተናግረዋል።
የሀዋሳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን በበጀት ዓመቱ ወደ ተለያዩ ሀገራት ከላካቸው ምርቶች ከ45 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱንም አቶ ማቲዮስ አንስተዋል፡፡
ገቢው የተገኘው ወደ አውሮፓ፣ሰሜን አሜርካ፣ እስያና አፍርካ ውስጥ በሚገኙ 14 የገበያ መዳረሻዎች ከተላኩ ምርቶች መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በሀዋሳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ከዚህ ቀደም ሥራ ላይ ከነበሩ ኩባንያዎች በተጨማሪ የተለያዩ ኩባንያዎች ስምምነት ፈርመው ወደ ምርት ሂደት መግባታቸው ተገልጿል፡፡
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026