
ቦንጋ፤ ሐምሌ 23/2017(ኢዜአ)፦የሌማት ትሩፋት መርሀ ግብር የምግብ ዋስትናቸውን ከማረጋገጥ ባለፈ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እንዳሳደገው በካፋ ዞን የቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ።
የሌማት ትሩፋት መርሀ ግብር በቤተሰብና በሀገር ደረጃ በምግብ እራስን ለመቻል እየተደረገ ያለውን ጥረት ለማሳካት ከፍተኛ አበርክቶ አለው።
ይህም በዘርፉ የተሰማሩ ዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ከማሳደግ ባለፈ በገበያ የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠር እያገዘ ይገኛል።
በሌማት ትሩፋት መርሀግብር የተሰማሩት የቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች ለኢዜአ እንደገለጹት መርሀ ግብሩ የምግብ ዋስትናቸውን ከማረጋገጥ ባለፈ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደገው መጥቷል።
ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል ወጣት ዋቅጅራ ግብጣም በተሰማራበት የሌማት ትሩፋት መርሀ ግብር 700 እንቁላል ጣይ ዶሮዎች በማርባት በቀን እስከ 600 እንቁላል ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረበ መሆኑን ተናግሯል።

ስራውንም በቀጣይ ለማስፋት በወተት ልማት፣ በእንስሳት እርባታ እና ማደለብ ሥራ ላይ ለመሰማራት ማቀዱንም ገልጿል።
ዘርፉ የቤተሰብን የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ትርፋማ ያደርጋል ያለው ወጣቱ ሌሎችም በስራው ላይ በመሰማራት ተጠቃሚ እንዲሆኑ መክሯል።

በዚሁ ከተማ የሚኖሩት የ68 ዓመት የእድሜ ባለፀጋው አቶ አወል አሊ በበኩላቸው የአንድ ቀን የዶሮ ጫጩቶችን በማሳደግ ለህብረተሰቡ ማሰራጨታቸውን ተናግረዋል።

ባለፉት ሰባት ወራት 3ሺህ የአንድ ቀን ጫጩቶችን ማሰራጨታቸውንና ለሦስተኛ ዙር 1ሺህ 500 ጫጩቶችን እያሳደጉ መሆናቸውን አክለዋል።
ወጣቶችም ይህን አርአያነት ያለው ተግባር በመከተል ከስራ ጠባቂነት ወጥተው ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እንዲያሳድጉ ልምዳቸውን ማካፈላቸውን ገልጸዋል።
የሌማት ትሩፋት መርሀ ግብር በከተማው የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ትልቅ አስተዋፅኦ እያደረገ መሆኑን የገለፁት ደግሞ የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ህብረት ሥራ ልማት ጽህፈት ቤት የእርባታ ሥራ ሂደት አስተባባሪ ወይዘሮ አታለለች ለገሰ ናቸው።

በከተማው 19 የወተት፣ የዶሮና የዓሣ መንደሮችን በማደራጀት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
የሌማት ትሩፋት በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ፋይዳው የጎላ መሆኑን ጠቁመው፣ ኢንሼቲቩ በእያንዳንዱ ግለሰብ ቤት ተግባራዊ እንዲሆን ሰፊ ሥራ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026