የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ኢትዮጵያ በቡና እና ስንዴ ምርታማነት ካስመዘገበቻቸው ስኬቶች የተሻለ ልምድ ወስደናል

Jul 31, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 23/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በቡና እና ስንዴ ምርታማነት ካስመዘገበቻቸው ስኬቶች የተሻለ ልምድ መውሰዳቸውን የዛምቢያ እና ናይጄሪያ የሥነ-ምግብ ባለሙያዎች ገለጹ።

በአዲስ አበባ ሲካሄድ የነበረው ሁለተኛው አለም አቀፍ የምግብ-ሥርዓት ጉባዔ ትናንት ተጠናቋል።

በጉባኤው የተለያዩ አገራት መሪዎች፣ የአለም አቀፍና አህጉራዊ ተቋማት ሃላፊዎች፣ የሥነ-ምግብ ባለሙያዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች ፣አምራችና ላኪዎችን ጨምሮ በርካታ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

ከጉባዔው ተሳታፊዎች መካከል የዛምቢያና የናይጄሪያ የሥነ-ምግብ ባለሙያዎች ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል።

ባለሙያዎቹ ኢትዮጵያ በግብርና ምርትና ምርታማነት ላይ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆኑ ተግባራትን ማከናወኗን ገልጸው፤ ይህንኑ ስኬት መስክ ድረስ ሄደው ማረጋገጣቸውን ነው የመሰከሩት።


የዛምቢያ የብሔራዊ የሥርዓተ-ምግብ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር ሙንታንጋ ካምፔንጌል (ዶ/ር) አገራቸው ከኢትዮጵያ የግብርና ሥራ በርካታ ልምዶችን መውሰዷን ነው ያስታወቁት።

ኢትዮጵያ የቡና መገኛ መሆኗን ተከትሎ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ባከናወነችው አመርቂ ተግባር ለውጭ ገበያ የምታቀርበውን ምርት በእጅጉ ማሳደግ መቻሏን አድንቀዋል።

ዛምቢያ ቡና አምራች ብትሆንም እንደ ኢትዮጵያ በብዛት የማምረት አቅም አለመገንባቷን ተናግረዋል።


ቡና ከምግብ-ሥርዓት ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ባይኖረውም ምርቱን በብዛት በማምረትና ለገበያ በማቅረብ ከሚገኘው ገቢ የምግብ ፍላጎትን ማሟላት እንደሚቻል ነው ያነሱት።

በናይጄሪያ የጤናና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የሥርዓተ-ምግብ ዳይሬክተር ላዲዲ አይቡሲ የኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ በርካታ ወጣቶችን ማሳተፉን መመልከታቸውን አንስተዋል።


አገራቸው በግብርና ዘርፉ በርካታ ወጣቶች እንዲሰማሩ ፍላጎት እንዳላትና ለዚህ ስኬት ከኢትዮጵያ ልምድ መውሰድ መቻላቸውን ነው የገለጹት።

የዛምቢያ የብሔራዊ የሥርዓተ-ምግብ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር ሙንታንጋ ካምፔንጌል (ዶ/ር) ስንዴ በበርካታ አገሮች ዋነኛ የምግብ ሰብል መሆኑን አንስተዋል።

ይሁን እንጂ አገራቸው ዛምቢያን ጨምሮ በርካታ የአፍሪካ አገራት አሁንም ድረስ ስንዴን ከውጭ እንደሚያስገቡ ነው ያስታወቁት።

በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ የስንዴ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ከራሷ አልፋ ወደ ውጪ መላክ መጀመሯ ትልቅ ስኬት ነው ብለዋል።

እንደ ስነ-ምግብ ባለሙያዎቹ ገለጻ፣ በቤተሰብ ደረጃ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን ለማዳረስ አገራት አነስተኛ ማሳ ያላቸውን አርሶ አደሮች መደገፍ አለባቸው።

በዚህ ረገድ የተገኘው ምርት ለተጠቃሚው እስኪደርስ ያለውን ሰንሰለት ቀልጣፋ በማድረግ የምግብ-ስርዓት ሽግግርን ማፋጠን እንደሚገባ አንስተዋል።

ሁለተኛው የአለም የምግብ-ሥርዓት ጉባዔ ኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነች ያለውን ሥራ በሚገባ ያሳየችበት መሆኑ መገለጹ ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ ነው -ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚው ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለአፍሪካ አገራት ትልቅ አርአያ ናቸው - የላይቤሪያ ልዑካን ቡድን

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...

Apr 16, 2026

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025