የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ ለሀገር ያለው ፋይዳ ዘርፈ ብዙ ነው

Oct 11, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤መስከረም 30/2018(ኢዜአ)፦የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ ለሀገር እድገት መፋጠን ዘርፈ ብዙ ፋይዳ እንዳለው የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ገለጸ፡፡

የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ በመላ አገሪቷ ነገ ይጀመራል።

በኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የአዲስ አበባ ስታቲስቲክስ ጽህፈት ቤት ስራ አስኪያጅ ተሰማ ኡርጌሳ ለኢዜአ እንዳሉት፥ በኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ የሚገኙ መረጃዎች በዘርፉ ለሚዘጋጁ እቅዶች፣ፖሊሲዎች እና ስትራቴጂዎች በትክክለኛ ግብዓት ያገለግላሉ።

የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ ጥናት ጠቃሚ የመረጃ ግብዓት በማስገኘት በኢኮኖሚያዊ ልማት ላይ ያለው አበርክቶ የጎላ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

እንደሥራ አስኪያጁ ገለጻ፤ በአዲስ አበባ ያሉ የንግድ ተቋማት እና ኢንዱስትሪዎች እና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ያሉባቸውን ችግሮች በመለየት ጥናት በማድረግ ለፖሊሲ ግብዓትነት እንዲውል ለማድረግ ያግዛል ነው ያሉት፡፡

በኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የቢዝነስ ስታቲስቲክስ መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ናቃቸው ነጋሽ በበኩላቸው፥ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ በሁሉም ክልሎች ያሉትን ድርጅቶች እና ሁሉንም የኢኮኖሚ አውታሮች ተደራሽ የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል።

በቆጠራ ስራው ለሚሰማሩ ባለሙያዎች ስልጠና የተሰጠ ሲሆን፤ ከጥቅምት 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በመላ ሀገሪቷ የቆጠራው የመስክ ስራ እንደሚጀመር ታውቋል፡፡

ሁሉም ዜጎችና የንግዱ ማኅበረሰብ የሚሰበሰበው መረጃ ለሀገር የሚጠቅም መሆኑን በመረዳት መረጃውን በመስጠትና በጎ ትብብር በማድረግ እንዲያግዙም ጥሪ አቅርበዋል፡፡

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ላለፉት 25 ቀናት በመላ ሀገሪቷ በ56 የስልጠና ማዕከላት ሲሰጥ የቆየው የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ ስልጠናን አጠናቋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026