🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 4/2018 (ኢዜአ)፡-ለኢትዮጵያ የልማት ዕቅዶች ትግበራ እያደረገ ያለውን ዘርፈ ብዙ ድጋፍ በቀጣይም በተለያዩ መስኮች አጠናክሮ እንደሚቀጥል ዓለም ባንክ አረጋግጧል።
በገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ የተመራ ከፍተኛ ልዑክ በዓለም ባንክ የምሥራቅ እና ደቡብ አፍሪካ ምክትል ፕሬዚዳንት ንዲያሜ ዲዮፕ ጋር ውጤታማ ውይይት አድርጓል።

በውይይቱ ላይ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር)፣የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማክሮ ኢኮኖሚ ከፍተኛ አማካሪ ተክለወልድ አጥናፉን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ ባለስልጣናት ተገኝተዋል።
በውይይታቸውም፥ ሁለቱ ወገኖች በኢትዮጵያ እየተካሄደ ስላለው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ፣ የፕሮጀክቶች ሂደት እና ለቀጣይ በሚኖሩ ዋና ዋና የትብብር ጉዳዮች ላይ መክረዋል።
አቶ አሕመድ በዚሁ ወቅት የዓለም ባንክ የኢትዮጵያን የልማት አጀንዳ በማሳደግ ረገድ ያለውን ወሳኝ ሚና አንስተው፥ለተደረገው እና በቀጣይም ለሚደረገው ከፍተኛ የቴክኒክ እና የገንዘብ ድጋፍ አመሥግነዋል።
ሰው ተኮርና ድህነት ቅነሳ ላይ እየተከናወኑ ስላሉ ውጤታማ ሥራዎች፣ በግብርና ምርታማነት፣ በኢነርጂ፣በሰብዓዊ ካፒታል ልማት እና በመሠረተ ልማት ዘርፎች የላቀ እገዛ እንደሚያስፈልግም አስገንዝበዋል።
ንዲያሜ ዲዮፕ በበኩላቸው፥ የኢትዮጵያ መንግሥት ለልማት እያሳየ ያለውን ቁርጠኛ አመራር እና አጠቃላይ ሂደት አድንቀዋል።

በመንግሥት ቁርጠኝነትም ሁሉን አቀፍ ማሻሻያ ፕሮግራም በጀመረ በአጭር ጊዜ ውስጥ ወሳኝ የሆኑ የማክሮ ኢኮኖሚ ግቦችን ማሳካት መቻሉን አንስተዋል።
በቀጣይም የዓለም ባንክ የኢትዮጵያን የልማት ዕቅዶች በተለያዩ መስኮች ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል።
በዚህም መሠረት በኢነርጂ፣በግብርናና የአነስተኛ አርሶ አደሮች ምርታማነት፣ የፋይናንስ አቅርቦት እና የእሴት ሰንሰለት ልማትን ለማሳደግ ዓለም ባንክ ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።
በተጨማሪም የሀገር ውስጥ ማኑፋክቸሪንግ ተነሳሽነትን እና የሀገር ውስጥ ምርትን ማሳደግ በሚሉት እና ሌሎች ጉዳዮች ላይ ድጋፉን እንደሚያጠናክር ነው የገለጹት።
የኢትዮጵያ የልማት መርሐ ግብሮች፣ የሀገሪቱ የእድገትና የዘላቂ ልማት ዋና ዋና አንቀሳቃሾች በተሳካ ሁኔታ ተፈፃሚ እንዲሆኑ የሁሉም አጋር አካላት ቀጣይነት ያለው ድጋፍ አስፈላጊ መሆኑን በማረጋገጥ ለቀጣይ ትብብር ያላቸውን ቁርጠኝነት ለማስቀጠል መግባባት ላይ ተደርሷል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025