🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 6/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የመስኖ ልማትና የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ ቁልፍ ሚና እየተጫወተ መሆኑን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳደር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) ገለጹ።
የአማራ ክልል የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የመስኖና የተቀናጀ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራዎች ንቅናቄ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር በደብረ ብርሃን ከተማ ልቼ ቀበሌ ተካሂዷል።

የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር)፣ በብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ይርጋ ሲሳይ፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ኃላፊ ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር) እና ሌሎች የክልሉ ስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ የመስኖ ልማትና የተቀናጀ የአካባቢ ጥበቃ ስራን በልዩ ትኩረት መምራት የሚያስችል ንቅናቄ በየዓመቱ የሚካሄድ መሆኑን ገልጸዋል።
የመስኖ ልማትና የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራ የግብርና ምርታማነትን ለማረጋገጥ ቁልፍ ተግባር ተደርጎ እየተሰራበት እንደሚገኝ ተናግረዋል።
የግብርና ምርታማነትን ለማሻሻል የሚተገበሩ የንቅናቄ መርሃ ግብሮችም የአፈር ለምነትን በማሻሻል፣ የአካባቢ ጥበቃን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የማይተካ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን ተናግረዋል።

በአማራ ክልል ያለውን በመስኖ ሊለማ የሚችል ሰፊ መሬት ታሳቢ በማድረግ በተቀናጀ ዕቅድ የግብርና ምርታማነትን ማሻሻል የሚያስችሉ ስራዎች በትኩረት እየተሰራባቸው እንደሚገኙ አንስተዋል።
በቀጣይም የግብርና ምርታማነት ውጤታማነትን የሚያረጋግጡ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስረድተዋል።
የደብረ ብርሃን ከተማ ተቀዳሚ ከንቲባ በድሉ ውብሸት፤ ለከተሞች መዘመንና መስፋፋት የተሰጠው ትኩረት ዕድሜ ጠገብ ታሪክ ላላት ደብረ ብርሃን ልዩ ዕድል መፍጠሩን ገልጸዋል።

የደብረ ብርሃን ከተማን ለማዘመን ከሚሰሩ ስራዎች በተጨማሪ በስንዴና ቢራ ገብስ ክላስተር የግብርና ሥርዓት ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስራዎች እየተሰሩ ነው ብለዋል።
የመስኖና የተቀናጀ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራዎች የማስጀመሪያ የንቅናቄ መርሃ ግብርም የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ የዜጎችን ህይወት ለማሻሻል ጉልህ ጠቀሜታ እንደሚያበረክት ተናግረዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025