የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በአማራ ክልል የመስኖ ልማትና የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ ቁልፍ ሚና እየተጫወተ ነው

Oct 17, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ጥቅምት 6/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የመስኖ ልማትና የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ ቁልፍ ሚና እየተጫወተ መሆኑን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳደር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) ገለጹ።

የአማራ ክልል የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የመስኖና የተቀናጀ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራዎች ንቅናቄ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር በደብረ ብርሃን ከተማ ልቼ ቀበሌ ተካሂዷል።


የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር)፣ በብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ይርጋ ሲሳይ፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ኃላፊ ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር) እና ሌሎች የክልሉ ስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ የመስኖ ልማትና የተቀናጀ የአካባቢ ጥበቃ ስራን በልዩ ትኩረት መምራት የሚያስችል ንቅናቄ በየዓመቱ የሚካሄድ መሆኑን ገልጸዋል።

የመስኖ ልማትና የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራ የግብርና ምርታማነትን ለማረጋገጥ ቁልፍ ተግባር ተደርጎ እየተሰራበት እንደሚገኝ ተናግረዋል።

የግብርና ምርታማነትን ለማሻሻል የሚተገበሩ የንቅናቄ መርሃ ግብሮችም የአፈር ለምነትን በማሻሻል፣ የአካባቢ ጥበቃን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የማይተካ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን ተናግረዋል።


በአማራ ክልል ያለውን በመስኖ ሊለማ የሚችል ሰፊ መሬት ታሳቢ በማድረግ በተቀናጀ ዕቅድ የግብርና ምርታማነትን ማሻሻል የሚያስችሉ ስራዎች በትኩረት እየተሰራባቸው እንደሚገኙ አንስተዋል።

በቀጣይም የግብርና ምርታማነት ውጤታማነትን የሚያረጋግጡ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስረድተዋል።

የደብረ ብርሃን ከተማ ተቀዳሚ ከንቲባ በድሉ ውብሸት፤ ለከተሞች መዘመንና መስፋፋት የተሰጠው ትኩረት ዕድሜ ጠገብ ታሪክ ላላት ደብረ ብርሃን ልዩ ዕድል መፍጠሩን ገልጸዋል።


የደብረ ብርሃን ከተማን ለማዘመን ከሚሰሩ ስራዎች በተጨማሪ በስንዴና ቢራ ገብስ ክላስተር የግብርና ሥርዓት ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስራዎች እየተሰሩ ነው ብለዋል።

የመስኖና የተቀናጀ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራዎች የማስጀመሪያ የንቅናቄ መርሃ ግብርም የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ የዜጎችን ህይወት ለማሻሻል ጉልህ ጠቀሜታ እንደሚያበረክት ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026