የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በአማራ ክልል የመስኖ ልማትና የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ ቁልፍ ሚና እየተጫወተ ነው

Oct 17, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ጥቅምት 6/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የመስኖ ልማትና የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ ቁልፍ ሚና እየተጫወተ መሆኑን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳደር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) ገለጹ።

የአማራ ክልል የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የመስኖና የተቀናጀ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራዎች ንቅናቄ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር በደብረ ብርሃን ከተማ ልቼ ቀበሌ ተካሂዷል።


የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር)፣ በብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ይርጋ ሲሳይ፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ኃላፊ ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር) እና ሌሎች የክልሉ ስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ የመስኖ ልማትና የተቀናጀ የአካባቢ ጥበቃ ስራን በልዩ ትኩረት መምራት የሚያስችል ንቅናቄ በየዓመቱ የሚካሄድ መሆኑን ገልጸዋል።

የመስኖ ልማትና የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራ የግብርና ምርታማነትን ለማረጋገጥ ቁልፍ ተግባር ተደርጎ እየተሰራበት እንደሚገኝ ተናግረዋል።

የግብርና ምርታማነትን ለማሻሻል የሚተገበሩ የንቅናቄ መርሃ ግብሮችም የአፈር ለምነትን በማሻሻል፣ የአካባቢ ጥበቃን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የማይተካ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን ተናግረዋል።


በአማራ ክልል ያለውን በመስኖ ሊለማ የሚችል ሰፊ መሬት ታሳቢ በማድረግ በተቀናጀ ዕቅድ የግብርና ምርታማነትን ማሻሻል የሚያስችሉ ስራዎች በትኩረት እየተሰራባቸው እንደሚገኙ አንስተዋል።

በቀጣይም የግብርና ምርታማነት ውጤታማነትን የሚያረጋግጡ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስረድተዋል።

የደብረ ብርሃን ከተማ ተቀዳሚ ከንቲባ በድሉ ውብሸት፤ ለከተሞች መዘመንና መስፋፋት የተሰጠው ትኩረት ዕድሜ ጠገብ ታሪክ ላላት ደብረ ብርሃን ልዩ ዕድል መፍጠሩን ገልጸዋል።


የደብረ ብርሃን ከተማን ለማዘመን ከሚሰሩ ስራዎች በተጨማሪ በስንዴና ቢራ ገብስ ክላስተር የግብርና ሥርዓት ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስራዎች እየተሰሩ ነው ብለዋል።

የመስኖና የተቀናጀ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራዎች የማስጀመሪያ የንቅናቄ መርሃ ግብርም የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ የዜጎችን ህይወት ለማሻሻል ጉልህ ጠቀሜታ እንደሚያበረክት ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026