የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በተያዘው በጀት ዓመት ከ3 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ስማርት ቴክኖሎጂዎችን ለደንበኞች ለማቅረብ ዝግጅት ተደርጓል - ኢትዮ ቴሌኮም

Oct 23, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 7/2018(ኢዜአ)፦ በተያዘው በጀት ዓመት ከ 3 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ስማርት የአገልግሎት ማሳለጫ ቴክኖሎጂዎችን ለደንበኞች ለማቅረብ ዝግጅት መደረጉን የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ ገለጹ።

የኢትዮ ቴሌኮም በኢትዮጵያ የኢንተርኔት ተደራሽነትን ይበልጥ ለማሳደግ የሚረዳ ዘኔክሰስ የተሰኘ አገልግሎት በይፋ አስጀምሯል።

የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ፥ የኢትዮጵያን ዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ እውን ለማድረግ ኢትዮ ቴሌኮም ለቴሌኮምና ዲጂታል መሰረተ ልማት ግንባታ ትኩረት መስጠቱን ተናግረዋል።

ባለፉት ስድስት ዓመታትም የአራተኛውና አምስተኛው ትውልድ ኔትወርክ አገልግሎት፣ ክላውድ፣ የቴሌብርና ዘመን ገበያን ጨምሮ ሥራ ላይ የዋሉ መሰረተ ልማቶች ትልቅ አቅም እየፈጠሩ መሆኑን ጠቅሰዋል።

የደንበኞችን ቁጥር ወደ 100 ሚሊዮን ለማድረስ ግብ መጣሉን ገልጸውም ከዚሁ ውስጥ 69 ሚሊዮን ደንበኞች የሞባይልና ብሮድባንድ ኢንተርኔት ተጠቃሚ ለማድረግ ስትራቴጂ ተነድፎ ወደ ሥራ መገባቱን አብራርተዋል።


በኢትዮጵያ 85 ነጥብ 9 ሚሊዮን የኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች እንዳሉ አመልክተው፤ ከእነዚህ ውስጥ 47 ሚሊዮኑ ብቻ ኢንተርኔትን እንደሚጠቀሙ አስታውቀዋል፡፡

ለዚህም የተለያዩ ምክንያቶች ቢኖሩም የመጠቀሚያ ስማርት መሳሪያዎች ዋጋ መወደድ ዋነኛው ምክንያት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

ኢትዮ ቴሌኮም ይህንኑ ታሳቢ በማድረግ ዘ ኔክሰስ የተሰኘ አገልግሎት ይፋ ማድረጉን ገልጸዋል፡፡

አገልግሎቱን ተደራሽ ለማድረግ የክላውድ ቴክኖሎጂን የሚጠቀሙ የእጅ ስልኮች፣ ላፕቶፖች፣ ታብሌቶችና ወርክ ስቴሽኖች በተመጣጣኝ ዋጋ ለገበያ ማቅረቡን ተናግረዋል።


መሳሪያዎቹን የሚጠቀሙ ደንበኞች የኢትዮ ቴሌኮምን ክላውድ በቀጥታ በመጠቀም አገልግሎት ማግኘት የሚያስችላቸው መሆኑንም አብራርተዋል፡፡

በተያዘው በጀት ዓመት ከ3 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ስማርት ቴክኖሎጂዎችን ለማቅረብ ዝግጅት መደረጉን ጠቁመው ይህም የኢንተርኔት ተደራሽነትን በከፍተኛ ሁኔታ ያሻሽላል ነው ያሉት።

በአሁኑ ወቅት ግብርና፣ ዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎት፣ ትምህርትን ጨምሮ የተለያዩ መንግሥታዊ አገልግሎቶች በኢንተርኔት እንደሚሰጡ ጠቁመው፤ በዚህ ረገድ ዘ ኔክሰስ አገልግሎት ወደ ስራ መግባት ትልቅ ፋይዳ አለው ብለዋል፡፡

ዘኔክሰስ አገልግሎት ተቋማትን ተወዳዳሪ ለማድረግ እንዲሁም ቀልጣፋ ዘመናዊ አገልግሎቶችን ተደራሽ እንዲያደርጉ ትልቅ ሚና እንደሚጫወትም አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026