የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ስታርት አፕ ለስራ እድል ፈጠራ እድገት የሚኖረውን አቅም ለመጠቀም ምቹ መደላድል እየተፈጠረ ነው 

Oct 23, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ጥቅምት 9/2018 (ኢዜአ)፡-ስታርት አፕ ለስራ እድል ፈጠራ እድገት የሚኖረውን አቅም ለመጠቀም ምቹ መደላድል እየተፈጠረ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ገለፁ።

የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ የስታርት አፕ ስነ ምኅዳሩን ማስፋት የሚያስችል የክህሎት ልማት እና አዳዲስ የስራ ዕድል ፈጠራን የሚያበረታቱ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው፡፡

አዳዲስ የፈጠራ ሃሳብ ያላቸው ወጣቶች የሚወዳደሩበት "ብሩህ ኢትዮጵያ" የክህሎት ውድድር ሀገራዊ ልማትን የሚያሳልጥና ስታርት አፖችን ማፍራት የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል፡፡


በዚህም ባለፉት አራት ዓመታት በሀገር አቀፍ ደረጃ 1 ሺህ 350 የፈጠራ ሀሳብ ላላቸው ዜጎች እውቅና ተሰጥቷል ብለዋል፡፡

በሀገሪቱ የሚኖረውን ፋይዳ አሟጦ ለመጠቀም አዳዲስ የፈጠራ ሀሳብ ላላቸው ስታርት አፖች የመስሪያ ቦታ፣ የፋይናንስ፣ የአቅም ግንባታና ሌሎች ድጋፎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል፡፡


የዜጎችን የስራ እድል ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ስታርት አፕ ወሳኝ መሆኑን በማንሳት፤ ስታርት አፖች ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን ገልጸዋል፡፡

በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የስታርት አፕ ዘርፍ ኃላፊ ሙልጌታ ውቤ በበኩላቸው፤የወጣቶች የስራ ፈጠራ ዝንባሌ እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡


መንግስት የወጣቶችን ተሳተፎ ለማሳደግና ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ የስታርት አፕ አዋጅ በማጽደቅ ወደ ሥራ ገብቷል ብለዋል፡፡

የፈጠራ ሀሳቦች ስታርት አፕ መሆናቸው በህግ ተለይቶ ምዝገባና ስያሜ ከተሰጠ በኋላ አስፈላጊው የፋይናንስና ሌሎች ጥቅማ ጥቅሞችን እንዲያገኙ እንደሚደረግ ገልጸዋል፡፡

አዋጁን ገቢራዊ ለማድረግ ሀገር አቀፍ የስታርት አፕ ፖርታል እየተዘጋጀ መሆኑን ገልጸው፤ የማስፈጸሚያ ደንቦችና መመሪያዎች ዝግጅት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.