🔇Unmute
ሐረማያ፤ ጥቅምት 10/2018(ኢዜአ)፦ የዩኒቨርሲቲ - ኢንዱስትሪ ትስስር የቴክኖሎጂና የእውቀት ሽግግር እንዲጎለብት በማድረግ ከፍተኛ ጠቀሜታ የሚያበረክት መሆኑን ምሁራን ገለጹ።
የምስራቅ ኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ-ኢንዱስትሪ ትስስር ፎረም ምስረታ በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ተካሂዷል።
በምክክሩ መድረክ ላይ የተሳተፉት ምሁራን ለኢዜአ እንደተናገሩት የዩኒቨርሲቲ - ኢንዱስትሪ ትስስር የምርምር ቴክኖሎጂና የእውቀት ሽግግር እንዲጎለብት ፋይዳው የላቀ ነው።

በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ሽግግርና ኢንዱስትሪ ትስስር አስተባባሪ ፈይሳ ሁንዴሳ እንዳሉት፤ ትስስሩ ከዚህ ቀደም ዩኒቨርሲቲዎችና - ኢንዱስትሪዎች በተበጣጠሰ መንገድ የሚያከናውኑት ስራዎችን ወጥ እንዲሆን የሚያስችል ነው።
ትስስሩም የዩኒቨርsiቲ ተማሪዎች በንድፈ ሀሳብ የቀሰሙትን እውቀት በኢንዱስትሪዎች የተግባር ልምምድ እንዲያገኙ የሚያስችል ነው ብለዋል።

ትስስሩ ኢንዱስትሪዎች የሚያጋጥማቸውን ችግሮች ለመፍታት ከዩኒቨርሲቲዎች ስልጠና፣ ማማከርና የምርምር ቴክኖሎጂ ውጤቶችን እንዲያገኙ ያስችላል ያሉት ደግሞ በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የኢንዱስትሪ ትስስርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክተር እሸቱ መኮንን(ዶ/ር) ናቸው።

በኦዳ ቡልቱ ዩኒቨርሲቲ የምርምር፣ ዓለም አቀፍ ግንኙነት እና አጋርነት ዳይሬክተር ጥምቀተ ዳኜ(ዶ/ር) በበኩላቸው የዩኒቨርሲቲ - ኢንዱስትሪ ትስስር ሀገራዊ የልማት እቅዶችን በጋራ ለማሳካት እገዛ ያደርጋል።
እንዲሁም የማህበረሰብ ችግሮችን በቅርበት ለመፍታትና የጋራ ችግሮችን አቅዶ በጋራ ለመቅረፍ ብሎም መፍትሄ ለማምጣት ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን አክለዋል።

ትስስሩ ዩኒቨርሲቲዎችን ከኢንዱስትሪዎች ጋር በማስተሳሰር በተግባርና ንድፈ-ሃሳብ የዳበረ የሰው ሃይል ለማፍራት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደርጋል ያሉት ደግሞ የድሬዳዋ ነጻ ንግድ ቀጣና ዋና ስራ አስኪያጅ አህመድ ረሺድ ናቸው።
በፎረም ምስረታው የምክክር መድረክ ላይ የሐረማያ፣ ድሬዳዋ፣ ሰመራ፣ ጅግጅጋ፣ ኦዳቡልቱምና ቀብሪደሃር ዩኒቨርሲቲዎች፣ የትምህርት ሞያ ስልጠና ኮሌጆች እንዲሁም በአካባቢው የሚገኙ የመንግስት እና የግል ኢንዱስትሪ ተወካዮች ተገኝተዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025