የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ከእንስሳት ሀብት የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግ በዘመናዊ እርባታና እና በእሴት ሰንሰለት ላይ የሚገጥሙ ችግሮች መፍታት ላይ ተኩረት ተደርጓል

Oct 29, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 18/2018 (ኢዜአ)፡- ከእንስሳት ሀብት የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግ ዘመናዊ የአረባብ ስርአትን መዘርጋት እና በእሴት ሰንሰለት ላይ የሚገጥሙ ችግሮችን መፍታት የርብርብ ማዕከላችን ነው ሲሉ የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ ገለጹ ፡፡

በተቀናጀ የእንስሳት ልማት፣ የስጋ ወጪ ንግድ፣ የእርድ እንስሳት አቅርቦት ትስስር ላይ የባለድርሻ አካላት የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው፡፡


የግብርና ሚኒስትር አቶ አዲሱ አረጋ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በዓለም ደረጃ ተጠቃሽ ቁጥር ያለው የእንስሳት ሀብት ቢኖራትም ተገቢውን ጥቅም እያገኘች አይደለም፡፡

ወደ ውጭ የሚላከውም ካለን አቅም አኳያ ዝቅተኛ ነው ያሉት ሚኒስትሩ በመስኩ ያሉ ችግሮችን በመፍታት ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ ርብርብ ይጠይቃል ብለዋል፡፡

የእንስሳት እርባታውን ዘመናዊ ማድረግ ሌላው የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን ገልጸው ዘመናዊ እንስሳት እርባታ ማዕከላትን ወደ ስራ ማስገባት በትኩረት እንደሚከናወን ጠቁመዋል፡፡

በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን በማንሳት፥ ዝርያ ማሻሻል ላይም የተሰሩ ስራዎች ለውጥ እያመጡ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

ለእንስሳት ምርት ማደግ የመኖ አቅርቦት ወሳኝ መሆኑን አመልክተው በመኖ አቅርቦት ላይ ባለሃብቱን በስፋት ለማሳተፍ የሚያስችል አሰራር እየተዘረጋ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

በእንስሳት አቅርቦት ውስጥ የደላላ ጣልቃ ገብነትን ጨምሮ የሚስተዋሉ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት የተጀመሩ ተግባራት እንደሚጠናከሩ አስረድተዋል፡፡

ቄራዎችንና ህብረት ስራ ማህበራትን በማገናኘት አቅርቦትን ለማሻሻል የሚያስችል ስልት መቀየሱንም ተናግረዋል፡፡

የእንስሳት ጤናን ማስጠበቅ በዘርፉ የሚገኘው ጥቅም ከፍ እንዲል የላቀ ፋይዳ እንዳለው የገለጹት ሚኒስትሩ በዚህም ላይ የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል፡፡


የግብርና ሚኒስቴር የእንስሳት እና ዓሳ ሀብት ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ፍቅሩ ረጋሳ በበኩላቸው የእንስሳት ዘርፍ ለምግብ ዋስትና መረጋገጥ እና ለስራ ዕድል ፈጠራ ትልቅ አቅም ያለው መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

በዚህ ረገድ የሚጠበቀውን ውጤት ለማረጋገጥ የባለድርሻ አካላት ቅንጅት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው ውይይቱ አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ ያለመ ነው ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026