የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የፋብሪካው መገንባት ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ያግዛል - ኮርፖሬሽኑ

Nov 6, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 26/2018(ኢዜአ)፡- የዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካ መገንባት ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት እንደሚያግዝ የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ገለጸ።

የዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካ በሀገር ውስጥ መገንባት ዘርፈ-ብዙ ጥቅም እንዳለው የኮርፖሬሽኑ የኮሙኒኬሽንና ማኅበራዊ ኃላፊነት ሥራ አመራር ሥራ አስኪያጅ ጋሻው አይችሉህም ገልጸዋል።

በዚህም መሠረት ከዚህ ቀደም በዩሪያ ማዳበሪያ አቅርቦት ላይ ከጊዜ፣ ከቦታ ርቀት፣ ከዋጋ፣ ከጥራት ወዘተ አኳያ ያጋጥሙ የነበሩ ችግሮችን መቅረፍ እንደሚያስችልም አብራርተዋል።

እንዲሁም እየጨመረ የመጣውን የአርሶ አደር እና በግብርና ዘርፍ የተሰማሩ ባለሃብቶች የዩሪያ ማዳበሪያ ፍላጎት ለማሟላት እንደሚያግዝ ለኢዜአ ተናግረዋል።

በሌላ በኩል ለዩሪያ አፈር ማዳበሪያ ግዥ ይወጣ የነበረውን የውጭ ምንዛሪ እንደሚያስቀርም ጠቁመዋል።

የግብርና ዘርፍን በይበልጥ በማሳደግ ወደ ውጭ የሚላኩ የግብርና ምርቶችን በስፋት ማምረት እንደሚያስችል ገልጸው፤ ከዚሁ ጋር በተያያዘም በግብርናው ዘርፍ የውጭ ገበያ ተወዳዳሪነትን በከፍተኛ ደረጃ ከፍ ያደርጋል ብለዋል።

የዩሪያ ማዳበሪያ በሚፈለግበት ጊዜ፣ ዋጋ እና መጠን በቅርበት ለማግኘት ማስቻሉም ሌላኛው ትሩፋት መሆኑን ነው የጠቀሱት።

የፋብሪካው መገንባት ሰፊ የሥራ ዕድል ለመፍጠርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ለማምጣትም ይጠቅማል ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መስከረም 22 ቀን 2018ዓ.ም የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ከዳንጎቴ ግሩፕ ጋር በመተባበር የሚገነባውን የዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካ የመሠረት ድንጋይ ማስቀመጣቸው ይታወሳል።

በ40 ወራት ተገንብቶ እንደሚጠናቀቅ የሚጠበቀው ይህ ፋብሪካ በዓመት 3 ሚሊየን ቶን የማምረት ዐቅም እንዳለውም ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026