🔇Unmute
ወልቂጤ፤ ጥቅምት 26/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ያጣችውን የባህር በር ባለቤትነት ለማስመለስ እያደረገች ያለውን ጥረት ያለ ልዩነት እንደሚደግፉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አስታወቀ።
የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጉዳይ የመልማት፣ የደህንነት እና ታሪካዊ ባለቤትነት ጉዳይ በመሆኑ ተገቢው ምላሽ እንዲገኝ ጥረቱ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
ይህንን በተመለከተም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሰሞኑን ተካሄዶ በነበረው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ ላይ ተገኝተው በመንግሥት አቋምና አቅጣጫዎች ላይ ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት ኢትዮጵያ የባሕር በር እንድታጣ የተደረገበትን ሁኔታ የሚገልፅ መረጃ ማግኘት አለመቻሉን አንስተዋል።
በጉዳዩ ዙሪያ ኢዜአ ከክልሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባላት ጋር ቆይታ ባደረገበት ወቅት ኢትዮጵያ ያጣችውን የባህር በር ባለቤትነት ለማስመለስ እያደረገች ያለውን ጥረት ያለ ልዩነት በአንድ ልብ እንደግፋለን ብለዋል።
የባሕር በር ለማግኘት እየተሄደበት ያለውን ዲፕሎማሲያዊ አካሄድ በመደገፍ አጀንዳው ተጠናክሮ እንዲቀጥል የበኩላቸውን ጥረት እንደሚያደርጉም አባላቱ አረጋግጠዋል።
አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ የጋራ ምክር ቤቱ አባላት መካከል የምክር ቤቱ ሰብሳቢ ደምስ ገብሬ እንዳሉት፤ ሀገራችን ህገወጥ በሆነ መንገድ የባህር በር ማጣቷ በትውልዱ ዘንድ ቁጭት ሆኖ የኖረ ጉዳይ ነው።
ያጣነውን የባሕር በር የማግኘት ጥያቄ ሁሉም ሀገር ወዳድ ዜጋ ሊረባረብበት የሚገባ ጉዳይ መሆኑንም አመልክተዋል።
ኢትዮጵያ በፍትሕ እና እውነታ ላይ ተመሥርታ የጠየቀችው የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ዓለም አቀፍ ሕጉ የሚደግፈውና ተቀባይነት ያለው በመሆኑ አጀንዳውን አጠናክሮ መቀጠል እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል።
ሀገራችን የባሕር በር የማግኘት ጥያቄዋ ያለ ፖለቲካዊ አመለካከት ልዩነት በመላ ኢትዮጵያውያን ተቀባይነት ያለው የሕልውና ጥያቄ ነው ሲሉ የገለፁት ደግሞ ሌላው የጋራ ምክር ቤቱ አባል ሄኖክ አብዱልሰመድ ናቸው።
የባህር በር ባለቤትነት የቅንጦት ሳይሆን ከ130 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ያላት ሀገር የኢኮኖሚና የደህንነት ብሎም የህልውና ጉዳይ መሆኑን አንስተዋል።
ሌላኛው የምክር ቤቱ አባል እንዳለ ኤርጌዶ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ከባሕር በር የራቀችበትን ምክንያት ለመጠየቅ የማይቻልበት ወቅት እንደነበረ አስታውሰዋል።
የባህር በር ባለቤትነት የሕልውና ጉዳይ መሆኑን በማንሳት የሀገር ዕድገትና ደህንነትን ለማረጋገጥ መንግስት እየሄደበት ያለው መንገድ የሚደግፍ ነው ብለዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025