🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 27/2018 (ኢዜአ)፡- የቻይና ባለሀብቶች በልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች እና ኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ያላቸው የኢንቨስትመነት ተሳትፎ እያደገ እንደሚገኝ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን አስታወቀ።
የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሰሃ ይታገሱ (ዶ/ር) በአልሙኒየም ዘርፍ ለመሰማራት ከፈለጉ የቻይና ባለሀብቶች ጋር ተወያይተዋል።
ባለሀብቶቹ ከፍተኛ ሀብት በሚጠይቀው አልሙኒየም ምርት ላይ ለመሰማራት ያቀዱ ሲሆን ኮርፖሬሽኑ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አመልክተዋል።
ውይይቱ የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሰሃ ይታገሱን (ዶ/ር) ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት ስራ ኃላፊዎችን ያካተተ የመንግስት ልዑካን ቡድን አባላት ከባለሀብቶቹ ጋር ባለፈው ሳምንት በቻይና ካደረገው ውይይት የቀጠለ መሆኑን አመልክተዋል።
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ ጳውሎስ በለጠ ኮርፖሬሽኑ በሚያስተዳድራቸው 13 ልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች እና አይሲቲ ፓርክን ጨምሮ በሶስት የኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ከ200 በላይ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ባለሀብቶች ተሰማርተው እንደሚገኙ ለኢዜአ ገልጸዋል።

38 በመቶ ድርሻ ከሚይዙት የውጭ ባለሀብቶች መካከል አብዛኞቹ ቻይናውያን መሆናቸውን ጠቅሰው በአልባሳት እና ጨርቃ ጨርቅ ዘርፍ በዋናነት መሰማራታቸውን አመልክተዋል።
የቻይና ባለሀብቶች አዳዲስ አማራጮችን በመመልከት በአሁኑ ሰዓት በምህንድስና (ኢንጂነሪንግ) መሰማራት መጀመራቸውን ጠቁመዋል።
ባለሀብቶቹ ካላቸው የኢንቨስትመንት ተሳትፎ ባሻገር በተለያዩ ዘርፎች ላይ ለመሰማራት ፍላጎት እያሳዩ ይገኛሉ ነው ያሉት።
ስሪላንካ፣ ጃፓን፣ አሜሪካ፣ ፈረንሳይ እና ኮሪያ ሪፐብሊክ በኢኮኖሚ ዞኖቹና ፓርኮቹ ተሰማርተው ከሚገኙ የውጭ ሀገራት ባለሀብቶች መካከል እንደሚጠቀሱም አመልክተዋል።
በአጠቃላይ ኮርፖሬሽኑ ሀገራዊ አቅምን የሚያግዙ የውጭ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ እየሰራ እንደሚገኝ አክለዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025