የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የቻይና ባለሀብቶች በልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች እና ኢንዱስትሪ ፓርኮች ያላቸው ተሳትፎ እያደገ መጥቷል

Nov 7, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 27/2018 (ኢዜአ)፡- የቻይና ባለሀብቶች በልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች እና ኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ያላቸው የኢንቨስትመነት ተሳትፎ እያደገ እንደሚገኝ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን አስታወቀ።

የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሰሃ ይታገሱ (ዶ/ር) በአልሙኒየም ዘርፍ ለመሰማራት ከፈለጉ የቻይና ባለሀብቶች ጋር ተወያይተዋል።

ባለሀብቶቹ ከፍተኛ ሀብት በሚጠይቀው አልሙኒየም ምርት ላይ ለመሰማራት ያቀዱ ሲሆን ኮርፖሬሽኑ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አመልክተዋል።

ውይይቱ የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሰሃ ይታገሱን (ዶ/ር) ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት ስራ ኃላፊዎችን ያካተተ የመንግስት ልዑካን ቡድን አባላት ከባለሀብቶቹ ጋር ባለፈው ሳምንት በቻይና ካደረገው ውይይት የቀጠለ መሆኑን አመልክተዋል።

የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ ጳውሎስ በለጠ ኮርፖሬሽኑ በሚያስተዳድራቸው 13 ልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች እና አይሲቲ ፓርክን ጨምሮ በሶስት የኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ከ200 በላይ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ባለሀብቶች ተሰማርተው እንደሚገኙ ለኢዜአ ገልጸዋል።


38 በመቶ ድርሻ ከሚይዙት የውጭ ባለሀብቶች መካከል አብዛኞቹ ቻይናውያን መሆናቸውን ጠቅሰው በአልባሳት እና ጨርቃ ጨርቅ ዘርፍ በዋናነት መሰማራታቸውን አመልክተዋል።

የቻይና ባለሀብቶች አዳዲስ አማራጮችን በመመልከት በአሁኑ ሰዓት በምህንድስና (ኢንጂነሪንግ) መሰማራት መጀመራቸውን ጠቁመዋል።

ባለሀብቶቹ ካላቸው የኢንቨስትመንት ተሳትፎ ባሻገር በተለያዩ ዘርፎች ላይ ለመሰማራት ፍላጎት እያሳዩ ይገኛሉ ነው ያሉት።

ስሪላንካ፣ ጃፓን፣ አሜሪካ፣ ፈረንሳይ እና ኮሪያ ሪፐብሊክ በኢኮኖሚ ዞኖቹና ፓርኮቹ ተሰማርተው ከሚገኙ የውጭ ሀገራት ባለሀብቶች መካከል እንደሚጠቀሱም አመልክተዋል።

በአጠቃላይ ኮርፖሬሽኑ ሀገራዊ አቅምን የሚያግዙ የውጭ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ እየሰራ እንደሚገኝ አክለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026