🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 30/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በበጀት አመቱ አራት ወራት ከ474ሺህ በላይ ዜጎች በሀገር ውስጥና በውጪ ሀገራት የስራ ዕድል እንደተፈጠረላቸው የክልሉ የስራ ዕድል ፈጠራና ክህሎት ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ምክትል ሀላፊ ዋስሁን ጎልጋ ለኢዜአ እንደተናገሩት በበጀት አመቱ በክልሉ የሚገኙ ስራ አጥ ዜጎችን የስራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ ነው።
በዚህም ከስራ አጥ ወጣቶች፣ ከወላጆች፣ ከኃይማኖት አባቶች፣ ከሀገር ሽማግሌዎች፣ ከአባ ገዳዎችና ከሃደ ሲንቄዎች ጋር የስራ ልየታና አመለካከት ላይ በማተኮር የግንዛቤ ማስረጽ ስራ መሰራቱን ተናግረዋል።
እንዲሁም መንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋርም ሰፊ መውይይት መደረጉንም ገልጸዋል።
በአጠቃላይ በበጀት አመቱ ለ2 ነጥብ 7 ሚሊዮን ዜጎች የስራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን አስታውሰው፤ ባለፉት አራት ወራት ከ474ሺህ በላይ ዜጎች በሀገር ውስጥና በተለያዩ የውጪ ሀገራት የስራ ዕድል መፍጠር መቻሉን አስታውቀዋል።
የስራ ዕድል ከተፈጠረላቸው ዜጎች መካከል 416ሺህ 995 የሚሆኑት በሀገር ውስጥ የስራ ዕድል ተጣቃሚ መሆናቸውን አንስተው፤ 58ሺህ 741 ዜጎች ደግሞ በቂ ስልጠና ተሰጥቷቸው የብቃት ማረጋገጫ በማግኘት ወደተለያዩ ሀገራት መሰማራታቸውን ገልጸዋል።
በተለይም በገጠሩ አካባቢ ወደ ስራ ለገቡ ዜጎች በስፋት በግብርና ልማት ኢንሼቲቮች መሳተፋቸውን አንስተው በከተማም ያሉትን አማራጮች ለመጠቀም ተሞክሯል ብለዋል።
የስራ ዕድሉ የተፈጠረው በኢንቨስትመንት፣ በጨርቃጨርቅ፣ በአገልግሎት፣ በግብርና ምርት ማቀነባበር፣ በጎጆ እንዱስትሪዎች፣ በብረታብረት፣ በእንጨትና እንጨት ውጤቶች ዘርፍ መሆኑን አብራርተዋል።
እንዲሁም በእንስሳት እርባታ፣ በወተት ልማት፣ በዶሮ እርባታ፣ በፍራፍሬና አትክልት ልማት መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል።
የስራ ዕድል የተፈጠረላቸው ዜጎች በሚሰማሩበት የስራ መስክ ውጤታማ እንዲሆኑ ክህሎት መር ስልጠና መሰጠቱን ጠቁመው ለሥራ ማስኬጃ የሚሆን ስምንት ቢሊዮን ብር ብድር መቅረቡን ተናግረዋል።
በተጨማሪም 15ሺህ ሄክታር መሬትና 2ሺህ 500 የማምረቻና መሸጫ ቦታዎች መሰጠቱን አስታውቀዋል።
በቀጣይም የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት የተጀመሩ ስራዎች ይጠናከራሉ ብለዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025