የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ አራት ወራት ከ474ሺህ በላይ የሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል ተጠቃሚ ሆነዋል

Nov 10, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 30/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በበጀት አመቱ አራት ወራት ከ474ሺህ በላይ ዜጎች በሀገር ውስጥና በውጪ ሀገራት የስራ ዕድል እንደተፈጠረላቸው የክልሉ የስራ ዕድል ፈጠራና ክህሎት ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው ምክትል ሀላፊ ዋስሁን ጎልጋ ለኢዜአ እንደተናገሩት በበጀት አመቱ በክልሉ የሚገኙ ስራ አጥ ዜጎችን የስራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ ነው።

በዚህም ከስራ አጥ ወጣቶች፣ ከወላጆች፣ ከኃይማኖት አባቶች፣ ከሀገር ሽማግሌዎች፣ ከአባ ገዳዎችና ከሃደ ሲንቄዎች ጋር የስራ ልየታና አመለካከት ላይ በማተኮር የግንዛቤ ማስረጽ ስራ መሰራቱን ተናግረዋል።

እንዲሁም መንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋርም ሰፊ መውይይት መደረጉንም ገልጸዋል።

በአጠቃላይ በበጀት አመቱ ለ2 ነጥብ 7 ሚሊዮን ዜጎች የስራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን አስታውሰው፤ ባለፉት አራት ወራት ከ474ሺህ በላይ ዜጎች በሀገር ውስጥና በተለያዩ የውጪ ሀገራት የስራ ዕድል መፍጠር መቻሉን አስታውቀዋል።

የስራ ዕድል ከተፈጠረላቸው ዜጎች መካከል 416ሺህ 995 የሚሆኑት በሀገር ውስጥ የስራ ዕድል ተጣቃሚ መሆናቸውን አንስተው፤ 58ሺህ 741 ዜጎች ደግሞ በቂ ስልጠና ተሰጥቷቸው የብቃት ማረጋገጫ በማግኘት ወደተለያዩ ሀገራት መሰማራታቸውን ገልጸዋል።

በተለይም በገጠሩ አካባቢ ወደ ስራ ለገቡ ዜጎች በስፋት በግብርና ልማት ኢንሼቲቮች መሳተፋቸውን አንስተው በከተማም ያሉትን አማራጮች ለመጠቀም ተሞክሯል ብለዋል።

የስራ ዕድሉ የተፈጠረው በኢንቨስትመንት፣ በጨርቃጨርቅ፣ በአገልግሎት፣ በግብርና ምርት ማቀነባበር፣ በጎጆ እንዱስትሪዎች፣ በብረታብረት፣ በእንጨትና እንጨት ውጤቶች ዘርፍ መሆኑን አብራርተዋል።

እንዲሁም በእንስሳት እርባታ፣ በወተት ልማት፣ በዶሮ እርባታ፣ በፍራፍሬና አትክልት ልማት መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል።

የስራ ዕድል የተፈጠረላቸው ዜጎች በሚሰማሩበት የስራ መስክ ውጤታማ እንዲሆኑ ክህሎት መር ስልጠና መሰጠቱን ጠቁመው ለሥራ ማስኬጃ የሚሆን ስምንት ቢሊዮን ብር ብድር መቅረቡን ተናግረዋል።

በተጨማሪም 15ሺህ ሄክታር መሬትና 2ሺህ 500 የማምረቻና መሸጫ ቦታዎች መሰጠቱን አስታውቀዋል።

በቀጣይም የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት የተጀመሩ ስራዎች ይጠናከራሉ ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026