የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

መገናኛ ብዙኃን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የመጠቀም ባህልን የሚያሳድጉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዘገባዎችን ማጠናከር አለባቸው

Nov 20, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሕዳር 9/2018(ኢዜአ)፦መገናኛ ብዙኃን የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የመጠቀም ባህልን የሚያሳድጉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዘገባዎች ማጠናከር እንደሚኖርባችው የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ገለጸ።

የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የልማት ሥራዎች የነገዋን ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት በሚያሳልጥ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ እንድትገኝ ያስቻሉ መሆናቸውን የኢዜአ አመራር አባላት ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) የሥራ ኃላፊዎችና የሙያተኞች ቡድን አባላትም በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና መስሪያ ቤት የቴክኖሎጂ ልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል።


የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር)፤ በአጭር ጊዜ ውስጥ 'ኢንተለጀንስ ለሁሉም' በሚል መሪ ሃሳብ በሁሉም ዘርፍ ውጤት እየተመዘገበ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ተቋማትም የዕለት ከዕለት ሥራዎቻቸውን በቀላሉ የሚያከናውኑበት ምቹ የቴክኖሎጂ ምኅዳር እየተፈጠረ እንደሚገኝ አንስተዋል።

የበርካታ ዓለም ሀገራት የመገናኛ ብዙኃንና ሌሎች ተቋማት አርቲፊሻል ኢንተለጀንስን በመጠቀም ጥራትና ፍጥነት ያላቸውን ተግባራትን በማከናወን ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል።


መገናኛ ብዙኃን የኢትዮጵያ ተቋማት የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የመጠቀም ባህል የሚያሳድጉበትን ግንዛቤ የሚያሳድጉ የዘገባ ስራዎችን መስራት እንደሚኖርባቸው ገልጸዋል።

ይህም ኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የፈጠራ መልካም አጋጣሚዎችን በመጠቀም የሙያተኞችን የሥራ ጫና የሚቀንሱበት ዕድል እንደሚፈጥር አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ዋና ስራ አስፈፃሚ ሰይፈ ደርቤ፤ በበኩላቸው በጉብኝቱ ላይ ኢትዮጵያ በዘርፉ በአፍሪካ ከፍ ያለ ስራ ለመስራት ምን እያከናወነች እንዳለች መመልከታቸውን ተናግረዋል።


የኢንስቲትዩቱ ጉብኝታቸውም በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ሌሎች መስኮች የኢትዮጵያን የብልጽግና ርዕይ የሚያሳካ ምቹ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ መደላድል እየተፈጠረ መሆኑን እንደታዘቡም ገልጸዋል።

በኢንስቲትዩቱም ታዳጊዎች የኢትዮጵያን መፃኢ እጣ ፋንታ በተሻለ ጉዞ ማጀብ የሚያስችል የፈጠራ ሥራ እያከናወኑ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በዚህም ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሀገራት ከውጭ የሚገባን ቴክኖሎጂ ብቻ የመጠቀም ባህል በመቀየር ለአህጉሪቷ ጭምር በአርዓያነት የሚጠቀስ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ፈጠራ ስራዎች እያከናወነች እንደምትገኝ መመልከታቸውን ጠቅሰዋል።


በጉብኝቱ የተሳተፉ የኢዜአ አመራር አባላትም፤ ኢትዮጵያ በአጭር ጊዜ ውስጥ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ለአፍሪካዊያን ጭምር ትምህርት የሚሰጥ አመርቂ ስኬት ማስመዝገቧን እንደታዘቡ ገልጸዋል።


በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የፈጠራ ሙያተኛን ለማፍራት የሚከናወኑ ተግባራትም የነገዋን ኢትዮጵያ የተሻለ ማድረግ በሚያስችል የትልም ጉዞ ላይ መሆኗንም ተናግረዋል።


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በኅዳር 07/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና መሥሪያ ቤት ሕንፃን መርቀው ስራ ማስጀመራቸው ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026