የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

መገናኛ ብዙኃን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የመጠቀም ባህልን የሚያሳድጉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዘገባዎችን ማጠናከር አለባቸው

Nov 20, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሕዳር 9/2018(ኢዜአ)፦መገናኛ ብዙኃን የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የመጠቀም ባህልን የሚያሳድጉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዘገባዎች ማጠናከር እንደሚኖርባችው የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ገለጸ።

የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የልማት ሥራዎች የነገዋን ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት በሚያሳልጥ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ እንድትገኝ ያስቻሉ መሆናቸውን የኢዜአ አመራር አባላት ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) የሥራ ኃላፊዎችና የሙያተኞች ቡድን አባላትም በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና መስሪያ ቤት የቴክኖሎጂ ልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል።


የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር)፤ በአጭር ጊዜ ውስጥ 'ኢንተለጀንስ ለሁሉም' በሚል መሪ ሃሳብ በሁሉም ዘርፍ ውጤት እየተመዘገበ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ተቋማትም የዕለት ከዕለት ሥራዎቻቸውን በቀላሉ የሚያከናውኑበት ምቹ የቴክኖሎጂ ምኅዳር እየተፈጠረ እንደሚገኝ አንስተዋል።

የበርካታ ዓለም ሀገራት የመገናኛ ብዙኃንና ሌሎች ተቋማት አርቲፊሻል ኢንተለጀንስን በመጠቀም ጥራትና ፍጥነት ያላቸውን ተግባራትን በማከናወን ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል።


መገናኛ ብዙኃን የኢትዮጵያ ተቋማት የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የመጠቀም ባህል የሚያሳድጉበትን ግንዛቤ የሚያሳድጉ የዘገባ ስራዎችን መስራት እንደሚኖርባቸው ገልጸዋል።

ይህም ኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የፈጠራ መልካም አጋጣሚዎችን በመጠቀም የሙያተኞችን የሥራ ጫና የሚቀንሱበት ዕድል እንደሚፈጥር አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ዋና ስራ አስፈፃሚ ሰይፈ ደርቤ፤ በበኩላቸው በጉብኝቱ ላይ ኢትዮጵያ በዘርፉ በአፍሪካ ከፍ ያለ ስራ ለመስራት ምን እያከናወነች እንዳለች መመልከታቸውን ተናግረዋል።


የኢንስቲትዩቱ ጉብኝታቸውም በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ሌሎች መስኮች የኢትዮጵያን የብልጽግና ርዕይ የሚያሳካ ምቹ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ መደላድል እየተፈጠረ መሆኑን እንደታዘቡም ገልጸዋል።

በኢንስቲትዩቱም ታዳጊዎች የኢትዮጵያን መፃኢ እጣ ፋንታ በተሻለ ጉዞ ማጀብ የሚያስችል የፈጠራ ሥራ እያከናወኑ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በዚህም ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሀገራት ከውጭ የሚገባን ቴክኖሎጂ ብቻ የመጠቀም ባህል በመቀየር ለአህጉሪቷ ጭምር በአርዓያነት የሚጠቀስ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ፈጠራ ስራዎች እያከናወነች እንደምትገኝ መመልከታቸውን ጠቅሰዋል።


በጉብኝቱ የተሳተፉ የኢዜአ አመራር አባላትም፤ ኢትዮጵያ በአጭር ጊዜ ውስጥ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ለአፍሪካዊያን ጭምር ትምህርት የሚሰጥ አመርቂ ስኬት ማስመዝገቧን እንደታዘቡ ገልጸዋል።


በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የፈጠራ ሙያተኛን ለማፍራት የሚከናወኑ ተግባራትም የነገዋን ኢትዮጵያ የተሻለ ማድረግ በሚያስችል የትልም ጉዞ ላይ መሆኗንም ተናግረዋል።


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በኅዳር 07/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና መሥሪያ ቤት ሕንፃን መርቀው ስራ ማስጀመራቸው ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ ነው -ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚው ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለአፍሪካ አገራት ትልቅ አርአያ ናቸው - የላይቤሪያ ልዑካን ቡድን

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...

Apr 16, 2026

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025