የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የመልካጀብዱን የአስፋልት መንገድ በቀጣይ ሁለት ወራት ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው

Nov 24, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ድሬዳዋ፤፤ ሕዳር 15/2018 (ኢዜአ)፡- የወጪና ገቢ ንግድን በማሳለጥ ለሀገር ዕድገት ወሳኝ ድርሻ ያለው የመልካጀብዱ የአስፋልት መንገድ ፕሮጀክት እየተፋጠነ መሆኑን የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የድሬዳዋ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት አስታወቀ።

የመንገዱ ግንባታ በቀጣይ ሁለት ወራት ሙሉ በሙሉ እንደሚጠናቀቅም ተመላክቷል።


በ1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በጀት በሁለት አቅጣጫ እየተፋጠነ የሚገኘው የመልካ ጀብዱ የመንገድ ፕሮጀክት፤ መልካጀብዱን ከድሬዳዋ እንዲሁም መልካን ከነፃ ንግድ ቀጠና ጋር በማስተሳሰር ወደ ጅቡቲ ከሚጓዘው የአስፋልት መንገድ ጋር የሚያገናኝ ፕሮጀክት ነው።

በወሰን ማስከበር ምክንያት ላለፉት ሰባት አመታት የተጓተተው ፕሮጀክት የድሬዳዋ አስተዳደር ካሳውን በመክፈል የፌደራል መንግስት መንገዱን ዳግም ወደ ስራ ማስገባቱን በዲስትሪክቱ የመልካጀብዱ ፕሮጀክት አስተባባሪ ኢንጂነር ደረሰ እሸቱ ለኢዜአ ገልጸዋል።


በአሁኑ ሰአትም የፕሮጀክቱ አካል የሆነ የ2 ነጥብ 1 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ የአንዱ አቅጣጫ ተጠናቅቆ ለተሽከርካሪዎች ክፍት መደረጉም ተጠቅሷል።

ፕሮጀክቱም 70 በመቶ መገባደዱ እና በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።

እንደ ኢንጂነር ደረሰ ገለፃ ይህ ፕሮጀክት የወጪና ገቢ የንግድ እንቅስቃሴዎች የሚዘወሩበት የድሬዳዋ ትልቁ የለውጥ መንገድ ነው።


ፕሮጀክቱ ድሬዳዋን ከጅቡቲ ጋር ከሚያስተሳስረው መንገድ ጋር የሚያገናኝ በመሆኑ ለድሬዳዋ እና ለሀገሪቱ ሁለንተናዊ ዕድገት አበርክቶው የጎላ መሆኑን ገልጸዋል።

የድሬዳዋ መልካ ጀብዱ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ፤ የመንገዱ መጠናቀቅ የወጪና ገቢ ንግድን በማሳለጥ የከተማዋን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እንደሚያፋጥን ገልጸዋል።


ወደ ጅቡቲ ሲጓዝ የነበረው የከባድ መኪና አሽከርካሪ ወጣት ኤፍሬም ወልደዮሐንስ ፤ መንገዱ በዚህ መልክ አምሮ መሰራቱ የመኪኖችን ደህንነት በማረጋገጥ ለተስተካከለ ትራፊክ ፍሰት ወሳኝ መሆኑን ተናግሯል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026