የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ስልጠናው በፈጠራ የታገዘ ተግባራትን ለማከናወን አግዞናል - የኮደርስ ሰልጣኞች

Nov 28, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ወልዲያ፤ ሕዳር 19/2018(ኢዜአ)፡- በኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የተመቻቸላቸውን ዕድል በመጠቀም በፈጠራ የታገዘ ተግባራትን ለማከናወን እንዳገዛቸው በሰሜን ወሎ ዞን የኮደርስ ሰልጣኞች ገለጹ።

የ "አምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ" ስልጠና ኢንሼቲቭ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ይፋ የተደረገ የዲጂታል ክሕሎት ማሳደጊያ መረሃ ግብር ነው።

"ትውልድ ይማር፣ ይሰልጥን ፣ ከዓለም ጋር ይፎካከር" በሚል እሳቤ መርሃ ግብሩ በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች እየተካሄደ

ሲሆኑ፤ ከእነዚህም በአማራ ክልል የሰሜን ወሎ ዞን ይገኝበታል።

በሰሜን ወሎ ዞን ባለፉት አራት ወራት ከሁለት ሺህ በላይ ወጣቶችና ሌሎች የሕብረተሰብ ክፍሎች የኮደርስ ስልጠናን በብቃት በማጠናቀቅ የማረጋገጫ ሰርቲፊኬት መውሰዳቸውን የዞኑ አስተዳደር አስታውቋል።

ስልጠናውን ካጠናቀቁት መካከል የዞኑ የመንግሰት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ባለሙያ የሆኑት ታደሰ አብዬ ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት፤ ስልጠናው በፈጠራ የታገዘ ተግባራትን ለማከናወን አቅም ፈጥሮልኛል ብለዋል።

በተለይ የኮምፒውተር ስራን አቅልሎ ለመስራትና ከወረቀት የተላቀቀ ዲጂታላይዜሽን አሰራርን መተግበር የሚያስችል እውቀት እንዳገኙበት ተናግረዋል።

የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የአገልግሎት አስጣጥን የሚያቀላጥፍ ነው ያሉት ደግሞ ሌላው ሰልጣኝ አቶ ሰለሞን አሰፋ ናቸው።


ስልጠናው ሁለት ወራት እንደወሰደባቸው ጠቅሰው፤ ቀደም ሲል ያላወቅኳቸውን የመረጃ አያያዝና ሌሎች ዕውቀቶችን እንዳገኝ አግዞኛል ብለዋል።

ስልጠናው ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠትና የመልካም አስተዳደርን ማስፈን የሚያስችል በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አመልክተዋል።

በሰሜን ወሎ ዞን አስተዳደር የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቡድን መሪ አማኑኤል ሮብሶ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ሕብረተሰቡን በተለይም ወጣቱን በኮደርስ ስልጠና ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ነው።

የመርሃ ግብሩ ዓላማ ወጣቱ ትውልድ እንዲሁም አመራሩና ሠራተኛው በዲጂታል ኢኮኖሚ ውስጥ መሳተፍ የሚያስችላቸውን የዲጂታል ክህሎት እንዲኖራቸው ለማመቻቸት እንደሆነ ገልጸዋል።

በበጀት ዓመቱም ከ25ሺህ በላይ የሕብረተሰብ ክፍሎችን በኮደርስ ለማሰልጠን ታቅዶ በተደረገ ጥረት በአራት ወራት ውስጥ ከሁለት ሺህ በላይ ማሰልጠን መቻሉን አስታውቀዋል።

በፕሮግራሚንግ ልማት፣ በዳታ ሳይንስ፣ በአንድሮይድ ማበልፀግና በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ መሠረታዊ ከህሎትን ለማስጨበጥ የተሰጠውን ስልጠና ላጠናቀቁ ሰርትፍኬት እንዲያገኙ መደረጉን ተናግረዋል።

በቀሪ ወራትም የስልጠና ማዕከላትን በማስፋት የታቀደውን ለማሳካት ሁሉን አቀፍ ጥረት እንደሚደረግ ገልጸዋል።

ለስልጠናው ስኬት በዞንና በወረዳ የሚገኙ የአይ ሲቲ ማዕከላት፣ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችና የወልዲያ ዩኒቨርሲቲ አይሲቲ ማዕከላት አገልግሎት እየሰጡ መሆኑም ተመልክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026