🔇Unmute
ደብረብርሃን፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ የደብረ ብርሃን ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ተኪና የውጭ ምንዛሬን የሚያስገኙ ምርቶችን በስፋት በማምረት የሀገሪቱን እድገት ለማፋጠን የድርሻውን እየተወጣ መሆኑን አስታወቀ።
የልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ ሥራ አስኪያጅ የሺጥላ ሙሉጌታ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በኢኮኖሚ ዞኑ ውስጥ ካሉ ስምንት ሼዶች መካከል በስድስቱ ኢንዱስትሪዎች ገብተው በማምረት ላይ ይገኛሉ።
ቀሪዎቹን በቅርቡ ለባለሀብቶች ለማሸጋገር እየተሰራ ነው ብለዋል።
በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ አራት ወራት የተመረተ ከ7 ነጥብ ሁለት ሚሊዮን በላይ የአሜሪካን ዶላር ግምት ያለው የቢራ ብቅል ለፋብሪካዎች መቅረቡን አስታውቃል።

በኢኮኖሚ ዞኑ በሚገኘው ቡርቱማልት የብቅል ፋብሪካ ተመርቶ ለቢራ ፋብሪካዎች በማቅረብ ከውጭ የሚገባን በመተካት የውጭ ምንዛሪ መዳን መቻሉ ተናግረዋል።
እንዲሁም በልዩ የኢኮኖሚ ዞን ተመርተው ወደ ውጭ ከተላኩ የጨርቃጨርቅና አልባሳት 676ሺህ 523 የአሜሪካን ዶላር የውጭ ምንዛሪ መገኘቱንም ገልጸዋል።
በተጨማሪም ተኪ ምርት በማምረትና የአርሶ አደሩን ምርት በግብአትነት በመጠቀም የገበያ ትስስር በመፍጠር አስተዋጽኦ ማበርከታቸውንም አንስተዋል።
ከሀገር ውስጥ አምራች ኢንዱስትሪዎችና ከአርሶ አደሮች ጋርም የገበያ ትስስር መፈጠሩን ጠቅሰዋል።
የደብረ ብርሃን ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ተኪ እና የውጭ ምንዛሬ የሚያስገኙ ምርቶችን በስፋት በማምረት የድርሻውን እየተወጣ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በኢኮኖሚ ዞኑ ከሚሰሩ ኢንዱስትሪዎች መካከል በሻንግ ቼንግ የጨርቃጨርቅ ፋብሪካ የሰው ሀብት ተቆጣጣሪና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጅ ባለሙያ ወጣት ውብሸት ሳፋቶ እንዳለው፤ ፋብሪካው ምርቱን በጥራት እና በብዛት በማምረት ወደ ውጭ እየላከ ይገኛል።
ሀይማኖት ብርሃኑ በበኩላቸው ከሁለት ዓመት በላይ በፋብሪካው ተቀጥረው በመስራት የተሻለ የስራ ልምድና ክህሎት ማግኘታቸውን ተናግረዋል።
በደብረ ብርሃን ልዩ የኢኮኖሚ ዞን በአሁኑ ወቅት ከ3ሺህ በላይ ሰዎች የስራ እድል እንደተፈጠረላቸው ተመልክቷል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026