የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ልዩ የኢኮኖሚ ዞኑ ተኪ ምርቶችን በስፋት በማምረት የድርሻውን እየተወጣ ነው

Nov 28, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ደብረብርሃን፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ የደብረ ብርሃን ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ተኪና የውጭ ምንዛሬን የሚያስገኙ ምርቶችን በስፋት በማምረት የሀገሪቱን እድገት ለማፋጠን የድርሻውን እየተወጣ መሆኑን አስታወቀ።

የልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ ሥራ አስኪያጅ የሺጥላ ሙሉጌታ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በኢኮኖሚ ዞኑ ውስጥ ካሉ ስምንት ሼዶች መካከል በስድስቱ ኢንዱስትሪዎች ገብተው በማምረት ላይ ይገኛሉ።

ቀሪዎቹን በቅርቡ ለባለሀብቶች ለማሸጋገር እየተሰራ ነው ብለዋል።

በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ አራት ወራት የተመረተ ከ7 ነጥብ ሁለት ሚሊዮን በላይ የአሜሪካን ዶላር ግምት ያለው የቢራ ብቅል ለፋብሪካዎች መቅረቡን አስታውቃል።


በኢኮኖሚ ዞኑ በሚገኘው ቡርቱማልት የብቅል ፋብሪካ ተመርቶ ለቢራ ፋብሪካዎች በማቅረብ ከውጭ የሚገባን በመተካት የውጭ ምንዛሪ መዳን መቻሉ ተናግረዋል።

እንዲሁም በልዩ የኢኮኖሚ ዞን ተመርተው ወደ ውጭ ከተላኩ የጨርቃጨርቅና አልባሳት 676ሺህ 523 የአሜሪካን ዶላር የውጭ ምንዛሪ መገኘቱንም ገልጸዋል።

በተጨማሪም ተኪ ምርት በማምረትና የአርሶ አደሩን ምርት በግብአትነት በመጠቀም የገበያ ትስስር በመፍጠር አስተዋጽኦ ማበርከታቸውንም አንስተዋል።

ከሀገር ውስጥ አምራች ኢንዱስትሪዎችና ከአርሶ አደሮች ጋርም የገበያ ትስስር መፈጠሩን ጠቅሰዋል።

የደብረ ብርሃን ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ተኪ እና የውጭ ምንዛሬ የሚያስገኙ ምርቶችን በስፋት በማምረት የድርሻውን እየተወጣ እንደሚገኝ ተናግረዋል።


በኢኮኖሚ ዞኑ ከሚሰሩ ኢንዱስትሪዎች መካከል በሻንግ ቼንግ የጨርቃጨርቅ ፋብሪካ የሰው ሀብት ተቆጣጣሪና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጅ ባለሙያ ወጣት ውብሸት ሳፋቶ እንዳለው፤ ፋብሪካው ምርቱን በጥራት እና በብዛት በማምረት ወደ ውጭ እየላከ ይገኛል።

ሀይማኖት ብርሃኑ በበኩላቸው ከሁለት ዓመት በላይ በፋብሪካው ተቀጥረው በመስራት የተሻለ የስራ ልምድና ክህሎት ማግኘታቸውን ተናግረዋል።

በደብረ ብርሃን ልዩ የኢኮኖሚ ዞን በአሁኑ ወቅት ከ3ሺህ በላይ ሰዎች የስራ እድል እንደተፈጠረላቸው ተመልክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.