🔇Unmute
ደብረብርሃን፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ የደብረ ብርሃን ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ተኪና የውጭ ምንዛሬን የሚያስገኙ ምርቶችን በስፋት በማምረት የሀገሪቱን እድገት ለማፋጠን የድርሻውን እየተወጣ መሆኑን አስታወቀ።
የልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ ሥራ አስኪያጅ የሺጥላ ሙሉጌታ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በኢኮኖሚ ዞኑ ውስጥ ካሉ ስምንት ሼዶች መካከል በስድስቱ ኢንዱስትሪዎች ገብተው በማምረት ላይ ይገኛሉ።
ቀሪዎቹን በቅርቡ ለባለሀብቶች ለማሸጋገር እየተሰራ ነው ብለዋል።
በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ አራት ወራት የተመረተ ከ7 ነጥብ ሁለት ሚሊዮን በላይ የአሜሪካን ዶላር ግምት ያለው የቢራ ብቅል ለፋብሪካዎች መቅረቡን አስታውቃል።

በኢኮኖሚ ዞኑ በሚገኘው ቡርቱማልት የብቅል ፋብሪካ ተመርቶ ለቢራ ፋብሪካዎች በማቅረብ ከውጭ የሚገባን በመተካት የውጭ ምንዛሪ መዳን መቻሉ ተናግረዋል።
እንዲሁም በልዩ የኢኮኖሚ ዞን ተመርተው ወደ ውጭ ከተላኩ የጨርቃጨርቅና አልባሳት 676ሺህ 523 የአሜሪካን ዶላር የውጭ ምንዛሪ መገኘቱንም ገልጸዋል።
በተጨማሪም ተኪ ምርት በማምረትና የአርሶ አደሩን ምርት በግብአትነት በመጠቀም የገበያ ትስስር በመፍጠር አስተዋጽኦ ማበርከታቸውንም አንስተዋል።
ከሀገር ውስጥ አምራች ኢንዱስትሪዎችና ከአርሶ አደሮች ጋርም የገበያ ትስስር መፈጠሩን ጠቅሰዋል።
የደብረ ብርሃን ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ተኪ እና የውጭ ምንዛሬ የሚያስገኙ ምርቶችን በስፋት በማምረት የድርሻውን እየተወጣ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በኢኮኖሚ ዞኑ ከሚሰሩ ኢንዱስትሪዎች መካከል በሻንግ ቼንግ የጨርቃጨርቅ ፋብሪካ የሰው ሀብት ተቆጣጣሪና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጅ ባለሙያ ወጣት ውብሸት ሳፋቶ እንዳለው፤ ፋብሪካው ምርቱን በጥራት እና በብዛት በማምረት ወደ ውጭ እየላከ ይገኛል።
ሀይማኖት ብርሃኑ በበኩላቸው ከሁለት ዓመት በላይ በፋብሪካው ተቀጥረው በመስራት የተሻለ የስራ ልምድና ክህሎት ማግኘታቸውን ተናግረዋል።
በደብረ ብርሃን ልዩ የኢኮኖሚ ዞን በአሁኑ ወቅት ከ3ሺህ በላይ ሰዎች የስራ እድል እንደተፈጠረላቸው ተመልክቷል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025