🔇Unmute
ደብረብርሃን ፤ ሕዳር 19/2018 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶችን ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ገበያን የማረጋጋት ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉን የዞኑ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ አስታወቀ።
የመምሪያው ሃላፊ ተወካይ ፈጠነ ሞገስ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በመንግስት ለገበያ ማረጋጋት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ መሰራቱ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ያለውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ እያደረገ ነው።
ባለፉት አራት ወራት ብቻ በሸማቾች ሕብረት ሥራ ማህበራት በኩል 429 ሚሊዮን ብር ተመድቦ ገበያ የማረጋጋት ሥራ መከናወኑን ገልጸዋል።

በዚህም 141 ሺህ ኩንታል ጤፍ፣ ማሽላ፣ ስንዴ፣ በቆሎና ሌሎች የግብርና ምርቶች እንዲሁም 38 ሺህ ኩንታል የኢንዱስትር ውጤቶችን ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ ማቅረብ መቻሉን ተናግረዋል።
በተጨማሪም ከ425 ሺህ ሊትር በላይ የምግብ ዘይት መቅረቡን ጠቁመው በቀጣይም ምርቶችን ለሸማቹ በተመጣጣኝ ዋጋ የማቅረቡ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
የመንግስት ሠራተኞች በሦስት ወር ክፍያ የሚፈልጉትን ምርት ወስደው እንዲጠቀሙ የሚያስችል አሰራር መዘርጋቱንም አስረድተዋል።
ከምርት አቅርቦት በተጨማሪ ያለአግባብ ምርት በሚደብቁና ዋጋ በሚጨምሩ ህገ ወጥ ነጋዴዎች ላይ ጥብቅ ክትትልና ቁጥጥር እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል።

በአጎለላና ጠራ ወረዳ የመንግስት ሠራተኞች ሸማች ህብረት ሥራ ማህበር ፀሀፊ አቶ አስፋው ንጋቱ እንደገለጹት፤ ማህበሩ 15 ሚሊዮን ብር በመመደብ 215 ኩንታል የዳቦ ዱቄትና ስኳር አቅርቧል።
በቅርቡ የበርበሬ ምርት ለማቅረብ ከአምራች አርሶ አደሮች ጋር የግዥ ውል መፈፀሙንም ጠቁመዋል።
ከተጠቃሚዎች መካከልም አቶ ልዑል ታደሰ ፤በህብረት ሥራ ማህበራት በኩል የሚቀርቡ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እየገዙ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በማህበራት ስኳር በገበያ ካለው ዋጋ በኪሎ እስከ 40 ብር፣ የዳቦ ዱቄት እስከ 20 ብር ቅናሽ እንዲሁም ሌሎች ምርቶችም በተመጣጣኝ ዋጋ እየቀረበላቸው መሆኑን ተናግረዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025