የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ምርቶችን ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ገበያን ለማረጋጋት እየተሰራ ነው

Nov 28, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ደብረብርሃን ፤ ሕዳር 19/2018 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶችን ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ገበያን የማረጋጋት ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉን የዞኑ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ አስታወቀ።

የመምሪያው ሃላፊ ተወካይ ፈጠነ ሞገስ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በመንግስት ለገበያ ማረጋጋት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ መሰራቱ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ያለውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ እያደረገ ነው።

ባለፉት አራት ወራት ብቻ በሸማቾች ሕብረት ሥራ ማህበራት በኩል 429 ሚሊዮን ብር ተመድቦ ገበያ የማረጋጋት ሥራ መከናወኑን ገልጸዋል።


በዚህም 141 ሺህ ኩንታል ጤፍ፣ ማሽላ፣ ስንዴ፣ በቆሎና ሌሎች የግብርና ምርቶች እንዲሁም 38 ሺህ ኩንታል የኢንዱስትር ውጤቶችን ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ ማቅረብ መቻሉን ተናግረዋል።

በተጨማሪም ከ425 ሺህ ሊትር በላይ የምግብ ዘይት መቅረቡን ጠቁመው በቀጣይም ምርቶችን ለሸማቹ በተመጣጣኝ ዋጋ የማቅረቡ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

የመንግስት ሠራተኞች በሦስት ወር ክፍያ የሚፈልጉትን ምርት ወስደው እንዲጠቀሙ የሚያስችል አሰራር መዘርጋቱንም አስረድተዋል።

ከምርት አቅርቦት በተጨማሪ ያለአግባብ ምርት በሚደብቁና ዋጋ በሚጨምሩ ህገ ወጥ ነጋዴዎች ላይ ጥብቅ ክትትልና ቁጥጥር እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል።


በአጎለላና ጠራ ወረዳ የመንግስት ሠራተኞች ሸማች ህብረት ሥራ ማህበር ፀሀፊ አቶ አስፋው ንጋቱ እንደገለጹት፤ ማህበሩ 15 ሚሊዮን ብር በመመደብ 215 ኩንታል የዳቦ ዱቄትና ስኳር አቅርቧል።

በቅርቡ የበርበሬ ምርት ለማቅረብ ከአምራች አርሶ አደሮች ጋር የግዥ ውል መፈፀሙንም ጠቁመዋል።

ከተጠቃሚዎች መካከልም አቶ ልዑል ታደሰ ፤በህብረት ሥራ ማህበራት በኩል የሚቀርቡ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እየገዙ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በማህበራት ስኳር በገበያ ካለው ዋጋ በኪሎ እስከ 40 ብር፣ የዳቦ ዱቄት እስከ 20 ብር ቅናሽ እንዲሁም ሌሎች ምርቶችም በተመጣጣኝ ዋጋ እየቀረበላቸው መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026