የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ኮሌጁ የገጠሩን ማህበረሰብ ችግር ለመፍታት የሚያስችሉ ተግባራት እያከናወነ ነው 

Nov 28, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ድሬደዋ፤ ሕዳር 19/2018 (ኢዜአ)፦የገጠሩን ማህበረሰብ ማህበራዊ ችግሮች ለመፍታት በተቀናጀ መንገድ እየሰራ መሆኑን በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ገለጸ።

ኮሌጁ በታዳሽ ኃይል ልማት ከሚሰራ ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር በማህበር ለተደራጁ የገጠር ወጣቶች በፀሐይ ኃይል የሚሰራ የእህል ወፍጮ አስረክቦ ወደ ስራ አስገብቷል።

የኢትዮ -ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ወጣቱ የአካባቢውን ፀጋዎች አልምቶ እራሱንና አካባቢውን እንዲለውጥ በክህሎት የታገዘ የተለያዩ ስልጠናዎች ተዳራሽ እያደረገ ይገኛል።


በእስካሁኑ እንቅስቃሴ ለ120 ወጣቶች ክህሎት መር ስልጠና መስጠቱን ጠቅሰው በፀሐይ ኃይል የሚሰራ የዘመናዊ ወፍጮ ባለቤት የተደረጉት የቃልቻ ገጠር ቀበሌ ወጣቶች የዚሁ ጥረት ማሳያ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ከጀርመን ተራድኦ ድርጅት በተገኘ ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ የተገዛውንና በፀሐይ ሐይል የሚሰራ ወፍጮ በአይነትና በጥራት በኮሌጁ ሰርቶ ማሳያዎች (ወርክሾፖች) በማባዛት በገጠር ቀበሌዎች ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

የገጠሩን ህብረተሰብ ማህበራዊ ችግሮች የሚፈቱትንና በፀሐይ ኃይል የሚሰሩ ወፍጮዎችን ለማባዛት በታዳሽ ኃይል ልማት ላይ ከሚሰሩ አጋር ድርጅቶች ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል።


ከዚህ በተጨማሪ በገጠር ቀበሌዎች ለሚገኙ ወጣቶች የተለያዩ የክህሎት ስልጠናዎችን በመስጠት በፈጠራ እና በክህሎት ታግዘው የአካባቢያቸውን ሃብቶች ወደ ጥቅም እንዲለውጡ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በኤሌክትሪክ መሳሪያዎች መገጣጠምና መጠገን ስልጠና የተሰጣቸው በማህበር የተደራጁ ወጣቶች በበኩላቸው እንዳሉት፤ ኮሌጁ የገጠሩን ማህበረሰብ ችግሮችን ለመፍታት እያደረገ የሚገኘው ስራ የሚበረታታ ነው።


የማህበሩ አባል ወጣት ጀማል ኢብራሂም እንደተናገረው ፤ በፀሐይ ኃይል የሚሰራ ወፍጮ ከበቂ ስልጠና ጋር ማግኘታቸው ቀጣዩን የህይወቸውን ምዕራፍ ለመምራት ያስችላቸዋል።

ይህን መሰል የተቀናጀ ድጋፍ ለወጣቶች ቢደረግ የወጣቱን ተስፋና ህይወት የበለጠ ለመለወጥ እንደሚያስችልም ነው የተናገረው።


የማህበሩ አባል ወይዘሮ ሩሚያ መሐመድ በበኩሏ፤ በኤሌክትሪክ ኃይል የሚሰራው ወፍጮ 24 ሰአታት ለህብረተሰቡ ተገቢውን አገልግሎት በመስጠት የነበረውን ችግር ለመፍታት እንደሚያስችልም ገልጻለች ።

እናቶች በውሃ እና በኤሌክትሪክ መቆራረጥ ምክንያት ይደርስባቸው የነበረውን ጫና ለመቀነስ ያግዛል ስትል ገልጻለች።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026