የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በምዕራብ ጎንደር ዞን ለበጋ መስኖ ልማት አስፈላጊ የግብርና ግብአቶች ቀርበዋል

Nov 28, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ገንዳ ውኃ፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ ለበጋ መስኖ ልማት የሚያስፈልጉ የግብርና ግብአቶችን በማቅረብ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን የምዕራብ ጎንደር ዞን የሕብረት ሥራ ማህበራት ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

የመተማ ገበሬዎች ሕብረት ሥራ ማህበራት ዩኒየን ከሰባት ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው የአፈር ማዳበሪያ ለመስኖ ልማቱ እያቀረበ መሆኑም ተመሏክቷል።

የጽህፈትቤቱ ኃላፊ ተወካይ ሲሳይ አለበል እንደገለጹት፣ዞኑ ለመስኖ ልማት የሚውል ሰፊ መሬት፣ ለበጋ መስኖ ልማት የሚስማማ የአየር ንብረትና ዓመቱን ሙሉ የሚፈሱ ወንዞች ባለቤት ነው።

በመሆኑም ይህን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም ለበጋ መስኖ ልማት አስፈላጊ ግብአቶችን በማቅረብ የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።


በልማቱም የአርሶ አደሩን ዘላቂ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመረው የግብአት አቅርቦት ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

በመስኖ የሚሳተፉ አርሶ አደሮች በየዓመቱ የግብዓት እጥረት ይገጥማቸው እንደነበር አስታውሰው፣ ዘንድሮ ችግሩን ለመፍታት በተደረገው ጥረትማዳበሪያ፣ ምርጥ ዘር፣ ፀረ ተባይና ኬሚካል ቀድሞ መቅረቡንአቶ ሲሳይ ተናግረዋል።

በመተማ ገበሬዎች ህብረት ሥራ ማህበራት ዩኒየን የቀረበው ማዳበሪያም በበጋ መስኖ ልማት የሚሳተፉ አርሶ አደሮችን ምርታማነት በማሳደግ ለገበያ የሚተርፍ ምርት ለማምረት የሚያስችል ነው።

የመተማ ገበሬዎች ህብረት ሥራ ማህበራት ዩኒየኑ ሥራ አስኪያጅ ሀብቴ ዘውዱ በበኩላቸው የበጋ መስኖ ልማትን በግብአት በመደገፍምርታማነትን ለማሳደግ በቅንጅት እየተሰራ ነው።

ለዚህም በተያዘው የበጋ ወቅት ለሚካሄደውየመስኖ ልማት ዩኒየኑ 2ሺህ 800 ኩንታል ዳፕ እና ዩሪያ ማዳበሪያ ማቅረቡን በማሳያነት ጠቅሰዋል።

በገንዳውኃ ከተማ ዙሪያ በመስኖ ልማት የተሰማሩት አርሶ አደር አብዱ ሁሴን እንደገለጹት በልማቱ በየዓመቱ ይገጥማቸው የነበረው የማዳበሪያ አቅርቦት እጥረት መፈታቱን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.