🔇Unmute
አምቦ፤ህዳር 29/2018(ኢዜአ)፦የአምቦ-ወሊሶ ኮንክሪት አስፋልት መንገድ ግንባታ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ገለጸ።
በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር አምቦ አካባቢ ፕሮጀክት ማኔጅመንት ጽህፈት ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዳኜ ለገሰ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ ከስድስት አመት በፊት ተጀምሮ ግንባታው የዘገየው የመንገዱ ግንባታ አሁን ላይ እየተፋጠነ ነው።

ከ 3 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ እየተከናወነ ያለው የመንገዱ ግንባታ 63 ነጥብ 78 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን መሆኑንም ተናግረዋል።
የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ እየተከናወነ ሲሆን የማማከርና የቁጥጥር ሥራውን ደግሞ የኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን እያከናወነው ይገኛል ብለዋል።
መንገዱ በሁለቱ ከተሞች መካከል ያለውን ግንኙነት እና የንግድ እንቅስቃሴ ከማሳለጡም የአካባቢው ነዋሪዎችም ምርታቸውን በቀላሉ ለገበያ እንዲያቀርቡ ያግዛልም ነው ያሉት።

ቀሪ የመንገድ ግንባታ ስራዎቹንም በሶስት ወራት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል።
በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ የአምቦ-ወሊሶ መንገድ ስራ አስኪያጅ አቶ ሺበሺ ጫካ፤ የመንገዱን ግንባታ ፈጥኖ በማጠናቀቅ የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ርብርብ እየተደረገ ነው ብለዋል።

የአምቦ-ወሊሶ መንገድ ግንባታ በአጭር ግዜ ለማጠናቀቅ ደቡብ ምዕራብ ሸዋንና ምዕራብ ሸዋን ከማገናኘት አልፎም የወንጪና የደንዲ ኢኮ ቱሪዝም ሎጆች ለሚደረጉ ጉዞዎችም ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ብለዋል።
ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ የአካባቢው ነዋሪዎች በበኩላቸው፤ የመንገዱ መጠናቀቅ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው ተናግረዋል።

በተለይም ወላድ እናቶችን ወደ ጤና ተቋማት ፈጥኖ ለማድረስ አስቸጋሪ እንደሆነ ጠቅሰው መንገዱ ሲጠናቀቅ ችግራቸውን የሚያቃልል በመሆኑ የመንገዱን መጠናቀቅ በጉጉት እየጠበቁ መሆኑን ተናግረዋል።
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025
ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...
Feb 8, 2025