🔇Unmute
አምቦ፤ህዳር 29/2018(ኢዜአ)፦የአምቦ-ወሊሶ ኮንክሪት አስፋልት መንገድ ግንባታ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ገለጸ።
በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር አምቦ አካባቢ ፕሮጀክት ማኔጅመንት ጽህፈት ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዳኜ ለገሰ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ ከስድስት አመት በፊት ተጀምሮ ግንባታው የዘገየው የመንገዱ ግንባታ አሁን ላይ እየተፋጠነ ነው።

ከ 3 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ እየተከናወነ ያለው የመንገዱ ግንባታ 63 ነጥብ 78 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን መሆኑንም ተናግረዋል።
የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ እየተከናወነ ሲሆን የማማከርና የቁጥጥር ሥራውን ደግሞ የኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን እያከናወነው ይገኛል ብለዋል።
መንገዱ በሁለቱ ከተሞች መካከል ያለውን ግንኙነት እና የንግድ እንቅስቃሴ ከማሳለጡም የአካባቢው ነዋሪዎችም ምርታቸውን በቀላሉ ለገበያ እንዲያቀርቡ ያግዛልም ነው ያሉት።

ቀሪ የመንገድ ግንባታ ስራዎቹንም በሶስት ወራት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል።
በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ የአምቦ-ወሊሶ መንገድ ስራ አስኪያጅ አቶ ሺበሺ ጫካ፤ የመንገዱን ግንባታ ፈጥኖ በማጠናቀቅ የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ርብርብ እየተደረገ ነው ብለዋል።

የአምቦ-ወሊሶ መንገድ ግንባታ በአጭር ግዜ ለማጠናቀቅ ደቡብ ምዕራብ ሸዋንና ምዕራብ ሸዋን ከማገናኘት አልፎም የወንጪና የደንዲ ኢኮ ቱሪዝም ሎጆች ለሚደረጉ ጉዞዎችም ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ብለዋል።
ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ የአካባቢው ነዋሪዎች በበኩላቸው፤ የመንገዱ መጠናቀቅ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው ተናግረዋል።

በተለይም ወላድ እናቶችን ወደ ጤና ተቋማት ፈጥኖ ለማድረስ አስቸጋሪ እንደሆነ ጠቅሰው መንገዱ ሲጠናቀቅ ችግራቸውን የሚያቃልል በመሆኑ የመንገዱን መጠናቀቅ በጉጉት እየጠበቁ መሆኑን ተናግረዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025