የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ማዕከሉ በምርምር የወጡ የተሻሻሉ የስንዴ ዝርያዎችን እያባዛ ለአርሶ አደሩ ተደራሽ እያደረገ ነው

Dec 11, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ፤ ታህሳስ 1/2018(ኢዜአ)፡- የቁሉምሳ ግብርና ምርምር ማዕከል በምርምር የወጡ የተሻሻሉ የስንዴ ዝርያዎች እያባዛ ለአርሶ አደሩ ተደራሽ እያደረገ እንደሚገኝ አስታወቀ።

በምርምር የወጡ የስንዴ ዝርያዎች በሄክታር እስከ 72 ኩንታል ምርት የሚሰጡ እንደሆኑ ተመልክቷል።

የምርምር ማዕከሉ ዳይሬክተር አቶ ሽመልስ አለማየሁ ለኢዜአ እንዳመለከቱት ፤ ማዕከሉ በሀገሪቱ የስንዴ ምርምር ብሔራዊ ማስተባበሪያ ሆኖ እየሰራ ይገኛል።


"መልካ፣ ጉቱ፣ አስጎሪ፣ ዳካ" እና ሌላም ስያሜ የተሰጣቸው የተለያዩ የተሻሻሉ የስንዴ ዝርያዎችን በማባዛት ለአርሶ አደሩ በማቅረብ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በምርምር የወጡ የስንዴ ዝርያዎች ቢጫ ዋግና የስንዴ ራስ አድርቅ በሽታዎችን በመቋቋም ከተለመደው የስንዴ ዝርያ የበለጠ ከፍተኛ ምርት መስጠት እንደሚችሉ በምርምር ሂደት ማረጋገጣቸውን አስረድተዋል።

የተሻሻሉት የስንዴ ዝርያዎች በማዕከሉ በሄክታር እስከ 72 ኩንታል፤ በአርሶ አደር ማሳ ደግሞ እስከ 61 ኩንታል በሄክታር መስጠት እንደሚችሉ አስረድተዋል።

በማዕከሉ እስከ አሁንም 113 የስንዴ ዝርያዎች በምርምር በማውጣት ለተጠቃሚዎች ተደራሽ መደረጉን ተናግረዋል።


ከዚህም ባለፈ ከወረር እና ከቢሾፍቱ ግብርና ምርምር ማዕከል ጋር በመተባበር 45 የማካሮኒ እና ፓስታ "ዱረም" የተሰኙ የስንዴ ዝርያዎች በምርምር ማውጣት መቻሉንም አንስተዋል።

የቁሉምሳ ግብርና ምርምር ማዕከል የሚያወጣቸውን የተሻሻሉ የስንዴ ዝርያዎቸን ለአርሶ አደሩ ተደራሽ የማድረጉን ተግባር አጠናክሮ መቀጠሉንም አስታውቀዋል።

ሀገሪቱ በምግብ ራስን በመቻል የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ያስቀመጠችውን ግብ ለማሳካት ማዕከሉ ከሌሎች መሰል ተቋማት ጋር በቅንጅት እየሰራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።


በዚህም የምርምር ማዕከሉ በግብርና ዘርፍ እየተተገበሩ ያሉትን ኢኒሼቲቮችና የሽግግር ሂደቱን በግንባር ቀደምትነት በቴክኖሎጂና አዳዲስ አሰራር እያገዘ ይገኛል ነው ያሉት።

በተጨማሪ ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ የስንዴ ዝርያዎችን በምርምር በማውጣት አባዝቶ መነሻ ዘር እያቀረበ እንደሚገኝም አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026