🔇Unmute
ጎንደር ፤ ታህሳስ 1/2018(ኢዜአ)፡- በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በአራት የወረዳ ዋና ከተሞች ህብረተሰቡን ያሳተፈ የኮሪደር ልማት ስራ መጀመሩን የዞኑ ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ አስታወቀ፡፡
በክልሉ የከተሞችን ገፅታ ለመቀየርና ልማታቸውን ለማፋጠን በባህር ዳር፣ በጎንደር፣ በደሴ፣ በደብረ ብርሃን፣ በኮምቦልቻ፣ በደብረ ማርቆስና በሌሎች ከተሞች የኮሪደር ልማቱ በፍጥነት እየተከናወነ ይገኛል።
በዞኖቹ ኮሪደር ልማት የተገኘውን ተሞክሮ በማስፋትም በወረዳ ከተሞችና በገጠር ኮሪደር ልማት በማስፋት እየተከናወነ መሆኑም ተመላክቷል።
የዚሁ ተግባር አካል የሆነው የኮሪደር ልማት በአይከል፣ በሻውራ፣ በቆላድባና በአምባ ጊዮርጊስ ከተሞች እየተከናወነ እንደሚገኝ የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ዳንኤል ወርቁ ተናግረዋል፡፡
በከተሞቹ እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ስራ ህብረተሰቡ 70 በመቶ የሚሆነውን ወጪ በራሱ ለመሸፈን ቃል በገባው መሰረት ወደ ስራ ተገብቷል ነው ያሉት።
የከተሞቹን የወደፊት እድገት ታሳቢ በማድረግ በተዘጋጀ ዲዛይን መሰረት ወደ ስራ መገባቱን ጠቁመው አመራሩና ባለሙያው ከጎንደር ከተማ የኮሪደር ልማት ስራ ልምድ እንዲቀስም ተደርጓል ብለዋል፡፡
የኮሪደር ልማቱ የከተሞቹ ለኑሮ፣ ለስራና ለትራፊክ እንቅስቃሴ እንዲሁም ለንግድ ስራ አመቺ ያልነበረውን ዲዛይን በመቀየር ትልቅ አቅም አለው ብለዋል።
በኮሪደር ልማቱ ጠባብ መንገዶችን የማስፋት፣ የእግረኛ መንገዶችንና አረንጓዴ ስፍራዎችን የመገንባት እንዲሁም የኮንቴይነር ሱቆችን በማንሳት ደረጃቸውን የጠበቁ የገበያ ቦታዎችን የማደራጀት ስራዎች እየተካሄዱ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡
ልማቱ የህብረተሰቡን የቆየ ልማዳዊ አስተሳሰብ በአዲስ በመቀየር ለስራ ያነሳሳ ትልቅ ተግባር ነው ያሉት ደግሞ የቆላድባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ታምራት አስረሳኸኝ ናቸው፡፡
ከተማ አስተዳደሩ የኮሪደር ልማት ስራው ለከተማው ልማትና እድገት መፋጠን የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ በመገንዘብ ህብረተሰቡን በማወያየት ወደ ስራ መግባቱን ተናግረዋል፡፡
ከተማውን በሚመጥን ደረጃ የተዘጋጀውን ዲዛይን መሰረት በማድረግ ወደ ስራ መገባቱን ጠቁመዋል፡፡
የኮሪደር ልማቱ ለከተሞች አዲስ ገጽታን በማላበስ ንጹህና አረንጓዴ ስፍራ አስፈላጊ መሆኑን በማህበረሰቡ ዘንድ ግንዛቤ የፈጠረ ታላቅ ተግባር ነው ያሉት የቆላድባ ከተማ ነዋሪ አቶ አስረስ አሸናፊ ናቸው፡፡
የከተማው ነባር ቤቶች የግንባታ አሰራር ለእሳት አደጋ ተጋላጭ የነበረ መሆኑን ጠቁመው፤ የኮሪደር ልማቱ የእሳት አደጋዎችን የሚቀንስና የሚያስቀር መሆኑን ተገንዝቤአለሁ ብለዋል፡፡
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025
ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...
Feb 8, 2025