የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የአብርሆት ቤተ-መጻሕፍትን ወደ ላቀ የዲጂታል ምዕራፍ የሚያሸጋግሩ ሦስት ታላላቅ የቴክኖሎጂ ፕሮጀክቶች ይፋ ሆኑ

Jan 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ታህሳስ 25/2018(ኢዜአ)፦የአብርሆት ቤተ-መጻሕፍትን ወደ ላቀ የዲጂታል ምዕራፍ የሚያሸጋግሩ ሦስት ታላላቅ የቴክኖሎጂ ፕሮጀክቶች ዛሬ በይፋ የማስጀመር ተግባር ተከናውኗል።

ይህንንም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአብርሆት ቤተ-መጻሕፍት በመገኘት የቴክኖሎጂ ፕሮጀክቶችን ዛሬ በይፋ አስጀምረዋል።

ከንቲባ አዳነች፥ አቤቤ የአብርሆት ቤተ-መጻሕፍት በመዲናዋ የንባብና የምርምር ባህል ማዕከል ሆኖ ስራ ከጀመረ አራት ዓመታት መቆጠራቸውን ገልጸዋል።


ዛሬ በቤተ-መጻሕፍቱ በመገኘትም፥ ተቋሙን ወደ ላቀ የዲጂታል ምዕራፍ የሚያሸጋግሩ ሦስት ታላላቅ የቴክኖሎጂ ፕሮጀክቶችን በይፋ ማስጀመራቸውን ጠቁመዋል።

በዓመት በአማካይ ለ1 ነጥብ 8 ሚሊዮን አንባቢዎች አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘውን ይህንን ተቋም ይበልጥ ለማዘመን የሚያስችሉ፦ የተቀናጀ የቤተ-መጻሕፍት አስተዳደር ሥርዓት፣ ዘመናዊ የዲጂታል ቤተ-መጻሕፍት እና ዓለም አቀፍ የምርምር መድረክ (Research Portal) በይፋ ሥራ እንዲጀምሩ መደረጉን አመልክተዋል።

አገልግሎቶቹ አብርሆት በአዲስ አበባ ብቻ የተገደበ እንዳይሆን ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥሩ የተናገሩት ከንቲባዋ ማንኛውም ተማሪም ሆነ ተመራማሪ በየትኛውም የኢትዮጵያ አካባቢ ሆኖ የአብርሆትን የዕውቀት ማዕድ መቋደስ እንዲችል ያደርጋሉ ነው ያሉት።

በተጨማሪም የታሪክ ሰነዶችን በዲጂታል መንገድ ተጠብቀው ለቀጣዩ ትውልድ እንዲተላለፉ ትልቅ እገዛ እንደሚኖራቸውም አክለዋል።

ከንቲባዋ ቴክኖሎጂዎቹን በማልማት አስተዋጽኦ ላበረከቱ ባለድርሻ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.