🔇Unmute
አሶሳ፤ ታህሳስ 27/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሳይንስ እና ፈጠራ ክህሎት ያላቸው ተማሪዎችን በመደገፍ ብቁና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።
ቢሮው "የተማሪዎች የሳይንስ እና ፈጠራ ሥራ ለልማታችን እመርታ" በሚል መሪ ሃሳብ የተማሪዎችን የፈጠራ አቅም ለማሣደግ ያለመ የምክክር መድረክ በአሶሳ ከተማ አካሂዷል።
በመድረኩ ላይ በተማሪዎች የተሰሩ የፈጠራ ስራዎች ለዕይታ ቀርበዋል።
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ የስርዓተ ትምህርት እና የተቋማት ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ሙሐመድ ኡስማን እንደገለፁት፣በሀገር ደረጃ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍን ለማሳደግ ለዘርፉ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል።

በዚህም ተማሪዎች ከትምህርታቸው ጎን ለጎን ችግር ፈቺ የፈጠራ ሥራዎችን በመስራት ራሳቸውን ከቴክኖሎጂ ጋር የሚያለማምዱበት ዕድል እየተፈጠረ ነው ብለዋል።
በክልሉ በርካታ ተማሪዎች የተለያዩ የፈጠራ ስራዎችን በመስራት በሀገር አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ መሆናቸውን ጠቁመው፤ ቢሮው የፈጠራ ክህሎት ላላቸው ተማሪዎች የተለያዩ መድረኮችን በማመቻቸት ስራዎቻቸውን እንዲያስተዋውቁ እያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።
በሀገር አቀፍ ደረጃ በተማሪዎች የፈጠራ ውድድር አሸናፊ ከነበሩት ተማሪዎች መካከል ተማሪ ብርሃኑ ሲሳይን እንደ ማሳያ ያነሱት አቶ ሙሐመድ፤ ሌሎች ተማሪዎችም ያላቸውን ተሰጥኦ እና ችሎታ በመጠቀም በሁሉም ዘርፍ ተወዳዳሪ መሆን እንደሚጠበቅባቸው መክረዋል።
ተማሪ ብርሃኑ ሲሳይ በፀሐይ ሃይል የሚሰራ የውሃ መሳቢያ ሞተር መሥራቱን በማስታወስ።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የማህበራዊ ዘርፍ አማካሪ አቶ ጌታቸው ፊሊጶስ በበኩላቸው፣ ኢትዮጵያ በዲጂታል 2030 ያለመችውን ዕቅድ ለማሣካት ከትምህርት ቤት ጀምሮ በዘርፉ ትኩረት ሰጥቶ መሥራት ይገባል ብለዋል።
ተማሪዎች ትልቅ ሀገራዊ ራዕይ ይዘው እንዲያድጉ እና የፈጠራ አቅሞቻቸውን አውጥተው ችግር ፈቺ ሥራዎችን እንዲሰሩ የሚያስችል የድጋፍና ክትትል ሥራ ከባለድርሻ አካላት እንደሚጠበቅም ገልጸዋል።
በመድረኩ ላይ የፈጠራ ስራዎቻቸውን ላቀረቡ ተማሪዎች ዕውቅና ተሰጥቷቸዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025