🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 28/2018(ኢዜአ)፡- ከተማርንና ዝግጁ ከሆንን በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ሂደት የማይናቅ ደረጃ ላይ እንደርሳለን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አስገነዘቡ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል በማስመልከት በተዘጋጀ የውይይት መድረክ ላይ ጽሑፍ አቅርበዋል።
ጽሑፍ ካቀረቡ በኋላም ከምሁራን ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በዚሁ ወቅትም፤መንግሥት የኮሪደር ልማትና መንገድ ሠርቶ ለነዋሪው ሲያቀርብ ይህን በአግባቡ እንዴት መያዝ እንደሚቻል ደግሞ ምሁራን ከተሜነትን የሰው ልጅ ዐዕምሮ ላይ መሥራት ይጠበቅባችኋል ብለዋል።
ከአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ጋር በተያያዘም ኢትዮጵያ ትልቅ ተስፋ ያላት ሀገር መሆኗን አንስተዋል።
ኤ አይ ከሚፈልጋቸው ነገሮች አንዱ ኢነርጂ መሆኑን ጠቁመው፤ ከዚህ አንጻር ኢትዮጵያ ብዙ የማምረት ዐቅም እንዳላት አረጋግጠዋል።
ኢነርጂ ላይ ኢንቨስት ካደረግን ለኤ አይ አንድ አስቻይ ጉዳይ ፈታን ማለት ነው ሲሉም ገልጸዋል።
ሌላው ኤ አይ የሚፈልገው ጉዳይ መረጃ(ዳታ) እና የመረጃ ማዕከል(ዳታ ሴንተር) መሆኑንም አስገንዝበዋል።
ከተማርን፣ ዝግጁ ከሆንን፣ እየሠራናቸው ያሉትንና በቀጣይ የምናከናውናቸውን ጨምሮ በመተባበር ለለውጥ ዝግጁ ሆነን በትጋት ከሠራን በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ሂደት የማይናቅ ደረጃ ላይ እንደርሳለን ብለዋል።
ለኤ አይ ግብዓት የሚሆኑ ነገሮች በብዛት በአፍሪካ እንደሚገኙም አስገንዝበዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025