የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በውጭ ምንዛሬ ማሻሻያ ትግበራ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን ከማሳደግ ባለፈ በህጋዊ እና ትይዩ ገበያ መካከል ያለውን ልዩነት ማጥበብ ተችሏል

Jan 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2018(ኢዜአ)፦ በውጭ ምንዛሬ ማሻሻያ ትግበራ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን ከማሳደግ ባለፈ በህጋዊ እና ትይዩ ገበያ መካከል ያለውን ልዩነት ማጥበብ ተችሏል ሲሉየብሔራዊ ባንክ ዋና ገዢኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

ባለፉት የሪፎርም ዓመታት የገንዘብ ፖሊሲን የማዘመን፣ የውጭ ምንዛሬ የማሻሻል ፣የፋይናንስ ዘርፍ ለውጥ እና የተቋማዊ ማሻሻያ ስራዎች ከተከናወኑ ዋና ዋና የማሻሻያ ተግባራት መካከል ተጠቃሽ መሆናቸውንም ገልጸዋል።

እነዚህ የማሻሻያ ተግባራት የዋጋ ግሽበትን በሰኔ 2012 ከነበረበት ከ30 በመቶ በታህሳስ 2018 ላይ ወደ 9.7 በመቶ ለመቀነስ አስችለዋል ብለዋል።

በውጭ ምንዛሬ ማሻሻያ ትግበራ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን ከማሳደግ ባለፈ በህጋዊ እና ትይዩ ገበያ መካከል ያለውን ልዩነት ማጥበብ ተችሏል ነው ያሉት።

አሁን ላይ ለግሉ ዘርፍ የሚቀርብ የብድር ድርሻ 77% መድረሱንም አስታውቀዋል። ዲጂታል አካውንቶችን በተመለከተም 254 ሚሊዮን አካውንቶች ማድረስ ያስቻለ ማሻሻያ መሆኑን ጠቁመዋል።

‎‎በቀጣይ የዋጋ ንረትን በነጠላ አሃዝ እንዲቆይ ማድረግ፣ የውጭ ምንዛሬ ገበያውን የበለጠ ተገማች እና የተረጋጋ ማድረግ፣የባንኮች ውህደት እና ግዢ ተግባራዊ ማድረግ፣ የኢንሹራንስ ዘርፉን የሚመራ ተቋምን ማደራጀት፣ የወለድ ነጻ የባንኪንግ ስርዓትን ማጠናከር ትኩረት ከሚደረግባቸው ጉዳዮች መካከል መሆናቸውን መናገራቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.