🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2018(ኢዜአ)፦ በውጭ ምንዛሬ ማሻሻያ ትግበራ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን ከማሳደግ ባለፈ በህጋዊ እና ትይዩ ገበያ መካከል ያለውን ልዩነት ማጥበብ ተችሏል ሲሉየብሔራዊ ባንክ ዋና ገዢኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
ባለፉት የሪፎርም ዓመታት የገንዘብ ፖሊሲን የማዘመን፣ የውጭ ምንዛሬ የማሻሻል ፣የፋይናንስ ዘርፍ ለውጥ እና የተቋማዊ ማሻሻያ ስራዎች ከተከናወኑ ዋና ዋና የማሻሻያ ተግባራት መካከል ተጠቃሽ መሆናቸውንም ገልጸዋል።
እነዚህ የማሻሻያ ተግባራት የዋጋ ግሽበትን በሰኔ 2012 ከነበረበት ከ30 በመቶ በታህሳስ 2018 ላይ ወደ 9.7 በመቶ ለመቀነስ አስችለዋል ብለዋል።
በውጭ ምንዛሬ ማሻሻያ ትግበራ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን ከማሳደግ ባለፈ በህጋዊ እና ትይዩ ገበያ መካከል ያለውን ልዩነት ማጥበብ ተችሏል ነው ያሉት።
አሁን ላይ ለግሉ ዘርፍ የሚቀርብ የብድር ድርሻ 77% መድረሱንም አስታውቀዋል። ዲጂታል አካውንቶችን በተመለከተም 254 ሚሊዮን አካውንቶች ማድረስ ያስቻለ ማሻሻያ መሆኑን ጠቁመዋል።
በቀጣይ የዋጋ ንረትን በነጠላ አሃዝ እንዲቆይ ማድረግ፣ የውጭ ምንዛሬ ገበያውን የበለጠ ተገማች እና የተረጋጋ ማድረግ፣የባንኮች ውህደት እና ግዢ ተግባራዊ ማድረግ፣ የኢንሹራንስ ዘርፉን የሚመራ ተቋምን ማደራጀት፣ የወለድ ነጻ የባንኪንግ ስርዓትን ማጠናከር ትኩረት ከሚደረግባቸው ጉዳዮች መካከል መሆናቸውን መናገራቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025
ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...
Feb 8, 2025