🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2018(ኢዜአ)፦ በውጭ ምንዛሬ ማሻሻያ ትግበራ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን ከማሳደግ ባለፈ በህጋዊ እና ትይዩ ገበያ መካከል ያለውን ልዩነት ማጥበብ ተችሏል ሲሉየብሔራዊ ባንክ ዋና ገዢኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
ባለፉት የሪፎርም ዓመታት የገንዘብ ፖሊሲን የማዘመን፣ የውጭ ምንዛሬ የማሻሻል ፣የፋይናንስ ዘርፍ ለውጥ እና የተቋማዊ ማሻሻያ ስራዎች ከተከናወኑ ዋና ዋና የማሻሻያ ተግባራት መካከል ተጠቃሽ መሆናቸውንም ገልጸዋል።
እነዚህ የማሻሻያ ተግባራት የዋጋ ግሽበትን በሰኔ 2012 ከነበረበት ከ30 በመቶ በታህሳስ 2018 ላይ ወደ 9.7 በመቶ ለመቀነስ አስችለዋል ብለዋል።
በውጭ ምንዛሬ ማሻሻያ ትግበራ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን ከማሳደግ ባለፈ በህጋዊ እና ትይዩ ገበያ መካከል ያለውን ልዩነት ማጥበብ ተችሏል ነው ያሉት።
አሁን ላይ ለግሉ ዘርፍ የሚቀርብ የብድር ድርሻ 77% መድረሱንም አስታውቀዋል። ዲጂታል አካውንቶችን በተመለከተም 254 ሚሊዮን አካውንቶች ማድረስ ያስቻለ ማሻሻያ መሆኑን ጠቁመዋል።
በቀጣይ የዋጋ ንረትን በነጠላ አሃዝ እንዲቆይ ማድረግ፣ የውጭ ምንዛሬ ገበያውን የበለጠ ተገማች እና የተረጋጋ ማድረግ፣የባንኮች ውህደት እና ግዢ ተግባራዊ ማድረግ፣ የኢንሹራንስ ዘርፉን የሚመራ ተቋምን ማደራጀት፣ የወለድ ነጻ የባንኪንግ ስርዓትን ማጠናከር ትኩረት ከሚደረግባቸው ጉዳዮች መካከል መሆናቸውን መናገራቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025