🔇Unmute
አዳማ፤ ጥር 13/2018(ኢዜአ)፦ የባዮና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የመኖ እጥረትን ለመፍታትና የእንስሳት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የጀመራቸውን የምርምር ሥራዎች የበለጠ ሊያጠናክር እንደሚገባ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት፣ሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሳሰበ።
የቋሚ ኮሚቴው አመራሮችና አባላት በአዳማ ከተማ በሚገኘው የባዮና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የምርምር ፕሮጀክቶች ላይ የመስክ ምልከታ አድርገዋል።
በዚህ ጊዜ በምክር ቤቱ የሰው ሀብት ልማት፣ ሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር)፤ ኢንስቲትዩቱ የህብረተሰቡን ችግር በተጨባጭ መፍታት የሚችሉ ምርምሮች ለማከናወን እያደረገ ያለውን ጥረት አድንቀዋል።

ደረቅ ቆሻሻን ወደ እንስሳት መኖና የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለመለወጥ የሚያስችል የፈጠራ ቴክኖሎጂ እውን ማድረጉ የዚህ ማሳያ መሆኑን በመጥቀስ።
በገጠርም ይሁን በከተማ በዶሮና ዓሳ እርባታ የተሰማሩ ወጣቶችና አርሶ አደሮች መኖን በቀላሉ በቤታቸው እንዲያዘጋጁ ድጋፍ በማድረግ የመኖ እጥረትን ለመፍታት የኢንስቲትዩቱ ሚና ወሳኝ መሆኑንም ነው ያብራሩት።

ኢንስቲትዩቱ ጠቃሚ የምርምር ውጤቶችን በማስፋፋት በባዮ ኢኮኖሚ ዕድገት ውስጥ ሚናውን የበለጠ እንዲያጎላም ጠይቀዋል።
መኖን በአገር ውስጥ ማምረት የውጭ ምንዛሬን በማስቀረት የእንስሳት ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድግ መሆኑን ጠቅሰው፣ ኢንስቲትዩቱ በዚህ ረገድ የጀመራቸውን የምርምር ሥራዎች የበለጠ አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።

የባዮና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ተመራማሪ ፍሬው ታፈሰ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ ኢንስቲትዩቱ ባለፉት ስምንት ወራት ቆሻሻን ወደ ከፍተኛ ፕሮቲን ያለው የእንስሳት መኖና የተፈጥሮ ማዳበሪያ የሚቀይር “ነብሳት” የተሰኘ ፕሮጀክት በመቅረፅ ውጤታማ ስራ ማከናወኑን ገልጸዋል።
ቴክኖሎጂው ፍራፍሬን ጨምሮ የግብርናና የኢንዱስትሪ ተረፈ ምርቶችን በመፍጨትና በማብላላት ወደ መኖና የተፈጥሮ ማዳበሪያ የሚቀይር መሆኑን አስረድተዋል።

አሁን ላይ በሳምንት 10 ኩንታል የዶሮ መኖ በማምረት በአዳማ ሰርቶ ማሳያና የስልጠና ጣቢያ የዶሮ እርባታ መጀመሩን ገልጸዋል።
የዶሮ መኖን ከተረፈ ምርት የማግኘት፣ የማላመድና የማሳደግ ተግባራትን ወደ ተጠቃሚው ለማሸጋገር በሂደት ላይ መሆኑን አመልክተዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026