የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ኢንስቲትዩቱ የመኖ እጥረትን ለመፍታት የጀመራቸውን የምርምር ሥራዎች የበለጠ ሊያጠናክር ይገባል

Jan 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ፤ ጥር 13/2018(ኢዜአ)፦ የባዮና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የመኖ እጥረትን ለመፍታትና የእንስሳት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የጀመራቸውን የምርምር ሥራዎች የበለጠ ሊያጠናክር እንደሚገባ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት፣ሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሳሰበ።

የቋሚ ኮሚቴው አመራሮችና አባላት በአዳማ ከተማ በሚገኘው የባዮና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የምርምር ፕሮጀክቶች ላይ የመስክ ምልከታ አድርገዋል።

በዚህ ጊዜ በምክር ቤቱ የሰው ሀብት ልማት፣ ሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር)፤ ኢንስቲትዩቱ የህብረተሰቡን ችግር በተጨባጭ መፍታት የሚችሉ ምርምሮች ለማከናወን እያደረገ ያለውን ጥረት አድንቀዋል።


ደረቅ ቆሻሻን ወደ እንስሳት መኖና የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለመለወጥ የሚያስችል የፈጠራ ቴክኖሎጂ እውን ማድረጉ የዚህ ማሳያ መሆኑን በመጥቀስ።

በገጠርም ይሁን በከተማ በዶሮና ዓሳ እርባታ የተሰማሩ ወጣቶችና አርሶ አደሮች መኖን በቀላሉ በቤታቸው እንዲያዘጋጁ ድጋፍ በማድረግ የመኖ እጥረትን ለመፍታት የኢንስቲትዩቱ ሚና ወሳኝ መሆኑንም ነው ያብራሩት።


ኢንስቲትዩቱ ጠቃሚ የምርምር ውጤቶችን በማስፋፋት በባዮ ኢኮኖሚ ዕድገት ውስጥ ሚናውን የበለጠ እንዲያጎላም ጠይቀዋል።

መኖን በአገር ውስጥ ማምረት የውጭ ምንዛሬን በማስቀረት የእንስሳት ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድግ መሆኑን ጠቅሰው፣ ኢንስቲትዩቱ በዚህ ረገድ የጀመራቸውን የምርምር ሥራዎች የበለጠ አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።


የባዮና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ተመራማሪ ፍሬው ታፈሰ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ ኢንስቲትዩቱ ባለፉት ስምንት ወራት ቆሻሻን ወደ ከፍተኛ ፕሮቲን ያለው የእንስሳት መኖና የተፈጥሮ ማዳበሪያ የሚቀይር “ነብሳት” የተሰኘ ፕሮጀክት በመቅረፅ ውጤታማ ስራ ማከናወኑን ገልጸዋል።

ቴክኖሎጂው ፍራፍሬን ጨምሮ የግብርናና የኢንዱስትሪ ተረፈ ምርቶችን በመፍጨትና በማብላላት ወደ መኖና የተፈጥሮ ማዳበሪያ የሚቀይር መሆኑን አስረድተዋል።


አሁን ላይ በሳምንት 10 ኩንታል የዶሮ መኖ በማምረት በአዳማ ሰርቶ ማሳያና የስልጠና ጣቢያ የዶሮ እርባታ መጀመሩን ገልጸዋል።

የዶሮ መኖን ከተረፈ ምርት የማግኘት፣ የማላመድና የማሳደግ ተግባራትን ወደ ተጠቃሚው ለማሸጋገር በሂደት ላይ መሆኑን አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026