የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግርን ለማፋጠን ያግዛል

Jan 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሮቤ፤ ጥር 14 /2018(ኢዜአ)፦የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ በዘርፉ የተገኙ ስኬቶችን ለማስቀጠልና የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግርን ለማፋጠን አጋዥ መሆኑን የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት አስታወቀ።

አገልግሎቱ በተለያዩ የሀገሪቷ አካባቢዎች በሚካሄደው 2ኛው ዙር የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ ላይ ለሚሰማሩ ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት ጀምሯል።

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የቴክኒክ አስተባባሪ ለሊሳ በሾ፣ በስልጠናው መክፈቻ ባደረጉት ንግግር፣ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ መካሄድ ውሳኔ ሰጪ አካላት ጥራት ያለውና መረጃን መሰረት ያደረገ ውሳኔ እንዲያሳልፉ ያግዛል።


በቆጠራው በመላው አገሪቱ የሚገኙ ከፍተኛ፣ መካከለኛና ዝቅተኛ ኢንተርፕራይዞች የሚካተቱ ሲሆን ቆጠራው በሁሉም ከተሞች ቤት ለቤት በመዞርና በገጠር ናሙና በመውሰድ ይከናወናል ብለዋል።

የኢኮኖሚ ድርጅቶቹ ቆጠራ በዘርፉ የተገኙ ስኬቶችን ለማስቀጠልና የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግርን ለማፋጠን እንዲሁም የፖሊሲ አማራጭ ሃሳቦችን ለማመንጨት ጉልህ ሚና እንዳለው አመልክተዋል።

ለኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራው የሚሳተፉ ከኦሮሚያ ክልል ከባሌ፣ ምሥራቅ ባሌ፣ምዕራብ አርሲ፣ምሥራቅ ቦረና እንዲሁም ከሶማሌ ክልል ሊበን ዞኖች የተወጣጡ 734 የዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠናው የሚሰጥ መሆኑን አንስተዋል።

ቆጠራው በዘርፉ ለሚዘጋጁ እቅዶች፣ ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ትክክለኛ ግብዓት ለማግኘት እንደሚያስችል ጠቅሰው፣ የስልጠናው ተሳታፊዎችም የአቅም ግንባታ ስልጠናውን በአግባቡ በመከታተል ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።


በኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የባሌ ጎባ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሽመልስ አሰፋ በበኩላቸው፣ ስልጠናው መረጃ ሰብሳቢዎች ጥራትና ወቅቱን የጠበቀ ተዓማኒነት ያለው መረጃ መሰብሰብ የሚችሉበትን ክህሎት እንዲያገኙ ያግዛል ብለዋል።

የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራው በመላው ኢትዮጵያ ከመስከረም 2018 ጀምሮ መካሄድ መጀመሩ ይታወቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ ነው -ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚው ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለአፍሪካ አገራት ትልቅ አርአያ ናቸው - የላይቤሪያ ልዑካን ቡድን

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...

Apr 16, 2026

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025