የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግርን ለማፋጠን ያግዛል

Jan 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሮቤ፤ ጥር 14 /2018(ኢዜአ)፦የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ በዘርፉ የተገኙ ስኬቶችን ለማስቀጠልና የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግርን ለማፋጠን አጋዥ መሆኑን የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት አስታወቀ።

አገልግሎቱ በተለያዩ የሀገሪቷ አካባቢዎች በሚካሄደው 2ኛው ዙር የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ ላይ ለሚሰማሩ ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት ጀምሯል።

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የቴክኒክ አስተባባሪ ለሊሳ በሾ፣ በስልጠናው መክፈቻ ባደረጉት ንግግር፣ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ መካሄድ ውሳኔ ሰጪ አካላት ጥራት ያለውና መረጃን መሰረት ያደረገ ውሳኔ እንዲያሳልፉ ያግዛል።


በቆጠራው በመላው አገሪቱ የሚገኙ ከፍተኛ፣ መካከለኛና ዝቅተኛ ኢንተርፕራይዞች የሚካተቱ ሲሆን ቆጠራው በሁሉም ከተሞች ቤት ለቤት በመዞርና በገጠር ናሙና በመውሰድ ይከናወናል ብለዋል።

የኢኮኖሚ ድርጅቶቹ ቆጠራ በዘርፉ የተገኙ ስኬቶችን ለማስቀጠልና የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግርን ለማፋጠን እንዲሁም የፖሊሲ አማራጭ ሃሳቦችን ለማመንጨት ጉልህ ሚና እንዳለው አመልክተዋል።

ለኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራው የሚሳተፉ ከኦሮሚያ ክልል ከባሌ፣ ምሥራቅ ባሌ፣ምዕራብ አርሲ፣ምሥራቅ ቦረና እንዲሁም ከሶማሌ ክልል ሊበን ዞኖች የተወጣጡ 734 የዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠናው የሚሰጥ መሆኑን አንስተዋል።

ቆጠራው በዘርፉ ለሚዘጋጁ እቅዶች፣ ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ትክክለኛ ግብዓት ለማግኘት እንደሚያስችል ጠቅሰው፣ የስልጠናው ተሳታፊዎችም የአቅም ግንባታ ስልጠናውን በአግባቡ በመከታተል ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።


በኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የባሌ ጎባ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሽመልስ አሰፋ በበኩላቸው፣ ስልጠናው መረጃ ሰብሳቢዎች ጥራትና ወቅቱን የጠበቀ ተዓማኒነት ያለው መረጃ መሰብሰብ የሚችሉበትን ክህሎት እንዲያገኙ ያግዛል ብለዋል።

የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራው በመላው ኢትዮጵያ ከመስከረም 2018 ጀምሮ መካሄድ መጀመሩ ይታወቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026