የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በኢትዮጵያ ተግባራዊ የተደረጉ የልማት ኢኒሼቲቮች ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ ጀምረዋል 

Feb 13, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ የካቲት 5/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ተግባራዊ የተደረጉ የልማት ኢኒሼቲቮች ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ መጀመራቸውን የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንትና የዋና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ ገለጹ።

የብልፅግና ፓርቲ እና የመንግሥት የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት የሥራ አፈጻጸም ድጋፋዊ ሱፐርቪዥን ማጠቃለያ መድረክ ተካሂዷል።

በመድረኩ ላይ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንትና የዋና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አደም ፋራህን ጨምሮ፣ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የሱፐርቪዥን ቡድኑ አባላት ተገኝተዋል።

በመድረኩ ላይ የሱፐርቪዥን አባላቱ በክልሎችና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች ባደረጉት ድጋፋዊ ሱፐርቪዥን ያገኟቸውን ውጤቶችና ተሞክሮዎች አቅርበዋል።

በዚህም መንግስት ተግባራዊ ያደረጋቸው የልማት ኢኒሼቲቮች የሕዝብን ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ አኳያ ውጤት እያስመዘገቡ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

በተለይም ተረጂነትን ለማስቀረት፣ የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ፣ በልማት ስራዎች፣ በግብርና ልማት፣ በኮሪደር ልማት፣ ከቴክኖሎጂ ሽግግር እና ከኢንዱትሪያላይዜሽን እንዲሁም ከሌሎች አኳያ ውጤታማ ስራዎች መከናወናቸው ተጠቅሷል።

በዚህ ወቅት የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ እንደተናገሩት፤ የዚህ ሱፐርቪዥን ዋነኛ ዓላማ በከፍተኛ አመራሮች ስልጠና ማጠቃለያ ላይ የተቀመጡ አቅጣጫዎችና የሥራ መመሪያዎች አፈጻጸም መገምገም ነው።


"በመደመር መንግሥት ዕይታ፣ የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሀሳብ በተሰጠው ስልጠና ማጠናቀቂያ ላይ ሀገራዊ ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች ላይ የተሰጡ ዝርዝር መመሪያዎች መሬት ላይ የወረዱበትን ሁኔታ ሱፐርቪዥኑ በዝርዝር መመልከቱንም ተናግረዋል።

በዚህም በክልሎችና በሁለቱም የከተማ አስተዳደሮች በተደረገው ምልከታ፤ መንግሥት ተግባራዊ ያደረጋቸው የልማት ኢኒሼቲቮች የሕዝብ ተጠቃሚነትን ከማረጋገጥ አኳያ አበረታች ውጤት እያስመዘገቡ መሆኑ መታየታቸውን ገልጸዋል።

በተለይም ተረጂነትን ለማስቀረት፣ የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ የተጀመሩ ጥረቶች፣ በግብርና፣ በኮሪደር ልማትና በኢንዱስትሪያላይዜሽን ዘርፎች የታዩ ውጤታማ ሥራዎች፣ ከቴክኖሎጂ ሽግግርና ከሌሎች የልማት ስራዎች አኳያ የተከናወኑ ተግባራት አበረታች መሆናቸውን ጠቅሰዋል።


የሱፐርቪዥን ቡድኑ የተሰጠውን ተልዕኮ በውጤታማነት ማከናወኑን ጠቅሰው፤ ስራዎች ከዕቅድ ባለፈ በተግባር መሬት ላይ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት መጀመራቸው የታየበት ትልቅ ግብዓት የተገኘበት ሂደት መሆኑን ተናግረዋል።

በቀጣይ በክልሎች መካከል የሚታየውን የአፈጻጸም ልዩነት ለማቀራረብና ተመሣሣይ ውጤት እንዲመዘገብ ለማድረግ በትኩረት እንደሚሠራ ገልጸዋል።

የአፈጻጸም ልዩነትን ለማቀራረብ ሦስት ዋና ዋና ስልቶች እንደሚተገበሩ ጠቁመዋል።

በዚህም ለጉዳዮች ባለቤት የማበጀት ተግባር እንደሚከናወን ጠቁመው፤ ተቋማት እንደየሥራ ባሕሪያቸው የወረዱ የልማት ኢኒሼቲቮችን ውጤታማነት የማረጋገጥ ኃላፊነት እንዲወስዱ ይደረጋል ብለዋል።

የተቋማትን ቅንጅት ማጠናከርም ሌላኛው ስልት መሆኑን ጠቅሰው፤ በሁሉም ኢኒሼቲቮች ላይ የተናበበ አሰራር እንዲኖር እንደሚሰራ አብራርተዋል።

በተመሣሣይ ቀጣይነት ያለው ድጋፍና ክትትልን በማጠናከር አፈጻጸምን የመከታተል፣ ስታንዳርድ የማበጀትና ማነቆዎችን የመፍታት ሥራ እንደሚከናወን ጠቁመዋል።

በክልሎች ባላቸው ጸጋ ልክ ሥራዎችን እንዲተገብሩና የሕዝብን ተጠቃሚነት እንዲያረጋግጡ የክትትልና የግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026