የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የክልሉን የልማት አቅም በመጠቀም የመሰረተ ልማት ችግሮችን ደረጃ በደረጃ በመፍታት ለህዝብ ጥያቄ ምላሽ እየተሰጠ ነው

Feb 13, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ታርጫ፤ የካቲት 5/2018(ኢዜአ)፦የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልልን የልማት አቅም በመጠቀም የመሰረተ ልማት ችግሮችን ደረጃ በደረጃ በመፍታት ለህዝብ ጥያቄ ምላሽ እየተሰጠ ነው ሲሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለፁ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤውን በታርጫ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።

በዛሬው ውሎው የምክር ቤት አባላቱ በልማት፣ በሰላምና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች በተደረገ ሰፊ ጥረት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል።

በተለይም ያደሩና የቆዩ የውሃ፣ የድልድይ፣ የመንገድና ሌሎች የመሰረተ ልማት ጥያቄዎችን ለመመለስ የተደረገው ሰፊ ርብርብ የሚበረታታና ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት መሆኑንም ገልፀዋል።


የክልሉ መንግስት የመሰረተ ልማት ችግሮችን ለመፍታት ያከናወናቸው ተግባራት የሚበረታቱ መሆኑን አባላቱ ጠቅሰው የገጠር ተደራሽ መንገዶችና ድልድዮች ግንባታ ላይ ትኩረት እንዲደረግም ጠይቀዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽ ፤ ክልሉ ያለውን አቅም በመጠቀም ቅድሚያ የሚሰጣቸውን የመሰረተ ልማት ችግሮች ደረጃ በደረጃ በመፍታት ለህዝብ ጥያቄ ምላሽ እየተሰጠ ነው ብለዋል።

ለዚህም በመንገድና ድልድይ መሰረተ ልማት ግንባታ ሂደት ውስጥ የማህበረሰቡ ተሳትፎና ድርሻ ትልቅ አቅም መሆኑን አንስተው ይህም ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።

ግንባታቸው በፌደራል መንግስት እየተከናወኑ የሚገኙ የአስፋልት መንገዶች እንዲፋጠኑ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅርበት እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።


በግብርናው ዘርፍም የምርጥ ዘር አቅርቦትን በማሻሻል ውጤታማ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፣ የህብረት ስራ ማህበራትን አቅም የማጠናከር ስራም ትኩረት እንደሚሰጠው ጠቁመዋል።

በክልሉ ከኮሪደር ልማት ጋር በማያያዝ ዘመናዊ ከተሞችን ለመፍጠር በሰፊው እየተሰራ መሆኑን አመልክተው መሰረተ ልማትን በማሟላትና በማስተር ፕላን የሚመሩ ከተሞችን እውን ከማድረግ አኳያ ስራዎች እየተሰሩ ነው ብለዋል።

ከማዘጋጃ ቤት፣ ከንግድና ከገቢ ጋር የሚገናኙ አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝ በማድረግ የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት የመሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎትን ለማስፋት የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ ነው -ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚው ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለአፍሪካ አገራት ትልቅ አርአያ ናቸው - የላይቤሪያ ልዑካን ቡድን

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...

Apr 16, 2026

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025