የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የባለብዙ ወገን አጀንዳዎች ላይ ያላቸውን አጋርነት ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆናቸውን ገለጹ

Mar 4, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2018(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ የፀጥታው ምክር ቤት ውክልናን ጨምሮ የባለብዙ ወገን አጀንዳዎች ላይ ያላቸውን ትብብር አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታወቁ።

39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የካቲት 7 እና 8 ቀን 2018 ዓ.ም በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ይካሄዳል።

የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከጉባኤው አስቀድሞ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ጋር ተወያይተዋል።

ውይይቱ በቀጣናዊ ሰላም እና ደህንነት፣ ዘላቂ ልማትና ሁሉን አቀፍ ኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን ላይ ያተኮረ ነው።

በተለይም የአፍሪካ የኢንዱስትሪ ዘርፍ፣ እሴት መጨመርና መዋቅራዊ ትራንስፎርሜሽን ለእድገት፣ ለስራ ፈጠራ እና ለዘላቂ መረጋጋት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወቱ ተነስቷል።

የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ የህብረቱ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አጋርነት ኢ-ተገማች በሆነው የዓለም ሁኔታ ውስጥ ሰላም፣ ደህንነትና ዘላቂ አጋርነትን ለማረጋገጥ ወሳኝ ነው ብለዋል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ የአፍሪካ ህብረት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የባለብዙ ወገን ስትራቴጂካዊ አጋር መሆኑን ገልጸው አፍሪካ በዓለም ሰላም፣ ደህንነትና የባለብዙ ወገን ስርዓት ሪፎርም ወሳኝ ሚና እንዳላት ተናግረዋል።

በውይይቱ የተመድ የፀጥታው ምክር ቤት አስቸኳይ ሪፎርም እንደሚያስፈልገውና አፍሪካ በምክር ቤቱ ቋሚ ውክልና ማግኘት እንደሚገባት ተነስቷል።

ባለስልጣናቱ ህብረቱ እና ተመድ የዓለም የፋይናንስ ስርዓት እንዲሻሻልና አፍሪካ ፍትሃዊ የፋይናንስ አቅርቦት እንድታገኝ የጀመሩትን የጋራ ስራ አጠናክረው ለመቀጠል መስማማታቸውን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026