የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የሰውሰራሽ አስተውሎት ትምህርትን ከአንደኛ ደረጃ ጀምሮ መስጠት የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ ነው

Mar 4, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2018(ኢዜአ)፦ የሰውሰራሽ አስተውሎትና የዲጂታል ክህሎት ማሳደጊያ ትምህርትን ከአንደኛ ደረጃ ጀምሮ መስጠት የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የትምህርት ሚኒስቴር ገለፀ።

በትምህርት ሚኒስቴር የኢ-ለርኒንግና የ5 ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ አስተባባሪ ሙሉነህ አጥናፉ ለኢዜአ እንዳሉት፥ በሀገሪቱ እየተተገበሩ ያሉ የሪፎርም ስራዎችን ለማሳለጥና ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ትግበራ ውጤታማነት የሰው ኃይል ልማት ወሳኝ ነው።

የኢትዮጵያን ብልፅግና ለማረጋገጥ የወጣቱን የዲጂታል፣ የሳይንስና ቴክኖሎጂ አቅም ማጎልበት ወሳኝ ነው

ለዚህም የዲጂታል ክህሎትና እውቀትን ማበልፀግ እንደሚያስፈልግ አንስተው ሚኒስቴሩ ሀገራዊ የሪፎርም አጀንዳዎችንና ተልዕኮውን መሰረት ያደረገ ጉዞ መጀመሩን ተናግረዋል።

የመምህራንና ተማሪዎችን እንዲሁም የህብረተሰቡን የዲጂታል እውቀትና ክህሎት ማሳደጊያ መርኃ ግብሮችን ለመተግበር እየተሰራ መሆኑንም ገልፀዋል።

በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ትኩረት ከተሰጣቸው ጉዳዮች አንዱ የሆነው የሰውሰራሽ አስተውሎት መሆኑን አንስተው ዘርፉ ለሀገሪቱ ኢኮኖሚ የሚያበረክተውን ጠቀሜታ ማረጋገጥ የሚያስችል ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል።

የሰውሰራሽ አስተውሎትና የዲጂታል ግንዛቤን የሚያሳድግ ትምህርት ከአንደኛ እስከ 12ኛ ክፍል ድረስ በስርዓተ ትምህርት ውስጥ በማካተት ለመስጠት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚገኙ መምህራንና ተማሪዎችን የዲጂታል ክህሎትና እውቀት ማሳደግ የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኝም ተናግረዋል።

ለዚህም የ5 ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠና እንዲወስዱ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ጨምረው አስረድተዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር ከዲጂታሉ ዓለም ጋር ብቁና ተወዳዳሪ ሆነው የሚራመዱ ታዳጊዎችንና ወጣቶችን ለማፍራት የዲጂታል እውቀትና ክህሎት መሠረቶች ላይ ትኩረት መስጠቱንም ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.