የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን አገልግሎቶቹን ሙሉ በሙሉ ዲጂታላይዝ አድርጓል

Mar 4, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2018 (ኢዜአ)፡- የሀገሪቱን የገቢና ወጪ ንግድ ሥርዓት ለማቀላጠፍና ቁጥጥሩን ለማዘመን አገልግሎቶቹን ሙሉ በሙሉ በዲጂታል ቴክኖሎጂ ማድረጉን የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ።

ኢትዮጵያ በዲጂታል 2025 ስትራቴጂ በርካታ ውጤታማ የዲጂታላይዜሽን ተግባራትን አከናውናለች። ይህንንም አጠናክሮ ለማስቀጠል የሚያስችለው ዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል።

ኢትዮጵያ ዲጂታል ሉዓላዊነቷን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነች ነው

በዲጂታል 2025 በርካታ ተቋማት አገልግሎታቸውን ያዘመኑ ሲሆን በአሁኑ ወቅት በዲጂታል የተደገፈ የተቀላጠፈ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛሉ።

የጉምሩክ ኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር አዘዘው ጫኔ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ኮሚሽኑ ዲጂታል 2025 ተከትሎ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ላይ አተኩሮ በርካታ ውጤታማ ተግባራት በማከናወን የሚሰጡ አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝ ማድረግ ተችሏል፡፡፡

በአሁኑ ወቅት ነጋዴዎች በማንኛውም ቦታ ሆነው የጉምሩክ ሥርዓትን መፈጸም የሚችሉበት የተቀናጀ የዲጂታል ሥርዓት መዘርጋት መቻሉን አስታውቀዋል።

ከ70 በላይ ተቋማትን በአንድ ላይ የሚያገናኘው የኤሌክትሮኒክ ሲንግል ዊንዶው ፕላትፎርም ተግባራዊ መድረጉን አንስተው፤ ይህም የንግድ ስራን ለማቀላጠፍ ትልቅ እመርታ መሆኑን ተናግረዋል።

የኮሚሽኑን የክትትል አቅም ለማሳደግ ስማርት ቦርደር ማኔጅመንት ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል ሲሉም አንስተዋል፡፡

የኤሌክትሮኒክ ካርጎ ትራኪንግ ሲስተምን በመጠቀም ጭነቶች ካለባቸው መስመር እንዳይወጡ ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ እንደሚገኝም ምክትል ኮሚሽነሩ አስታውቀዋል፡፡

በሰው ሰራሽ አስተውሎት የታገዙ ካሜራዎች በተለያዩ ስልታዊ ቦታዎች ላይ ተተክለው ውጤታማ አገልግሎት እየሰጡ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ምክትል ኮሚሽነሩ ኮሚሽኑ ከንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር፣ ከባንኮችና ከሌሎች ፈቃጅና ተቆጣጣሪ ተቋማት ጋር በቴክኖሎጂ ትስስር መፍጠሩን ገልጸዋል፡፡

በሀገር ውስጥ የታክስ ሥርዓትም የኢ-ፋይሊንግ እና የኢ-ፔይመንት አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ ስራ ላይ ውለዋል ብለዋል።

እንደ ምክትል ኮሚሽነሩ ገለጻ በአሁኑ ወቅት በጂቡቲ የሚገኙ ሁለት ቅርንጫፎችን ጨምሮ በመላ ሀገሪቱ ያሉ 15 ቅርንጫፎች በሙሉ በቴክኖሎጂ የተደገፈ የ24 ሰዓት አገልግሎት በቴክኖሎጂ በመስጠት ላይ ይገኛሉ።

ይህ መጠነ ሰፊ የዲጂታላይዜሽን ስራ የገቢና ወጪ ንግዱን ከማሳለጡ ባለፈ፣ የህግ ማስከበር ስራውን በቴክኖሎጂ የታገዘና ግልጽ አሰራረን ተግባራዊ በማድረግ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚደግፍ አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ ነው -ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚው ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለአፍሪካ አገራት ትልቅ አርአያ ናቸው - የላይቤሪያ ልዑካን ቡድን

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...

Apr 16, 2026

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025