🔇Unmute
ደብረብርሃን ፤ የካቲት 24/2018(ኢዜአ)፦በሌማት ትሩፋት መርሐግብር መሰማራታቸው ሀብት ለማፍራት እንዳስቻላቸው በሰሜን ሸዋ ዞን በእንስሳት ሃብት ልማት የስራ እድል የተፈጠረላቸው ማህበራት አስታወቁ።
የቡና ወጪ ንግድን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ለተቀናጀ ጥረት ትኩረት ተሰጥቷል
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሌማት ትሩፋት መርሐ ግብርን ጥቅምት 24 ቀን 2015 ዓ.ም በአርባ ምንጭ ከተማ ማስጀመራቸው ይታወሳል።
የመርሃ-ግብሩ ዋነኛ ግብ፤ የእንስሳት ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ እና የምግብ ስርዓትን ማሻሻልን ያለመ ነው።
በዚህም መሰረት በተለያዩ የሀገሪቷ አካባቢዎች ዜጎች በስጋ፣ በእንቁላል፣ በማር እና በወተት አምራችነት በስፋት በመሳተፍ ተጠቃሚ መሆን ችለዋል።
በአንጎለላና ጠራ ወረዳ በጎልባና ቃፌሮ ቀበሌ ሽመልስ ሙሉጌታና ጓደኞቹ የዶሮ እርባታ ማህበር ሰብሳቢ ዳዊት ሀይሌ፤ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ከስራ አጥነት ወደ ስራ ፈጣሪነትና ባለሀብትነት እንድንሸጋገር አድርጎናል ሲል ነው የገለጸው።
በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በሶስት ጫጩቶች የተጀመረው ስራ በአሁኑ ወቅት የጫጩቶቹን ቁጥር 6 ሺህ 500 ለማድረስ ችለናል ብሏል።
አራት ነጥብ አምስት ሚሊዮን ብር ካፒታል በማስመዝገብ ወደ ባለሃብትነት ለመሸጋገር እየሰሩ እንደሚገኙ ገልጿል።
በዚሁ ወረዳ የቆባ እንስሳት እርባታ ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ መላኩ ፀጋዬ እንደገለጹት፤ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የእንስሳት ዘርፉን ምርታማነትና ልማት ለማሳደግ እያስቻለ ነው።
አሁን ላይ 110 ዝርያቸው የተሻሻለ ላሞችን በመንከባከብ በቀን እስከ አንድ ሺህ ሊትር ወተት በማምረት ለአቀነባባሪዎች እያስረከቡ መሆናቸው ገልጸዋል።
ዘርፉን ለማዘመንና በቴክኖሎጂ የተደገፈ ለማድረግ በተደረገላቸው እገዛም በሁለት ነጥብ አምስት ሚሊዮን ብር ወጪ ግዥ መፈፀማቸውን ነው የገለጹት።
ከስደት መልስ ከጓደኞቿ ጋር በመደራጀት ስራ እንደጀመሩ የምትናገረው ብጽአት ጌታቸው ከመንግስት በተሰጣቸው ቦታ ሼድ በመገንባት የዶሮ እርባታ ስራውን ለማሳደግ እንደቻሉ ነው የምትናገረው።
የዶሮ እርባታ ስራው ላይ በመሳተፍም ሶስት ሚሊዮን ብር የሚሆን ካፒታል በማስመዝገብ ለሌሎች ወጣቶች የስራ እድል መፍጠር እንደቻሉ ነው የገለጸችው።
የሰሜን ሸዋ ዞን እንስሳትና ዓሳ ሃብት መምሪያ ኃላፊ አቶ ምትኩ ማሙሻ በበኩላቸው፤ በዞኑ በሌማት ትሩፋት የወተት፣ የእንቁላል፣ የስጋ፣ የማርና የዓሳ ምርትን በማሳደግ ገበያ የማረጋጋት ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል።
በዚህም ባለፉት ሰባት ወራት ተኩል የዓሳ፣ የወተት፣ የእንቁላል እንዲሁም የስጋና የማር ምርት በበቂ ሁኔታ በማምረት ገበያ የማረጋጋት ስራ መሰራቱን ገልጸዋል።
ባለፉት 7 ወራት ተኩል ከአንድ ሚሊዮን በላይ የአንድ ቀን ጫጩቶችን በዘርፉ ለተሰማሩ ወጣቶች ማሰራጨት መቻሉን ጠቁመው በሌማት ትሩፋት ከስምንት ሺህ በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች የስራ ዕድል ተፈጥሯል ብለዋል።
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025
ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...
Feb 8, 2025