የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤን ታስተናግዳለች

Mar 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ የካቲት 28/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ(ASMIS) ልታስተናግድ ነው።

ጉባኤውን የሚያዘጋጁት ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ (POA) እና ኤ.ጂ.ኤ ቴክ (AGA-Tech) ኢንተርፕራይዝ የጋራ መግለጫ ሰጥተዋል።

ጉባኤው እ.አ.አ ግንቦት 7 እና 8 ቀን 2026 በአዲስ አበባ የዓድዋ ድል መታሰቢያ እንደሚካሄድም አስታውቀዋል።

የመጀመሪያ የሆነው ይህ ጉባኤ የአፍሪካ ተፅዕኖ ፈጣሪ ድምፆችን ከመገናኛ ብዙኅን ድርጅቶች፣ ፖሊሲ አውጪዎችና የግሉ ዘርፍ መሪዎች ጋር የሚያገናኝ ታሪካዊ የጋራ መድረክ መሆኑ ተገልጿል።

''ተፅዕኖ ለተሻለች አፍሪካ'' በሚል መሪ ሃሳብ የሚካሄደው ጉባኤው የዲጂታል ተሳትፎ ፈጠራ፣ ቴክኖሎጂና ኃላፊነት ላይ ምክክር የሚደረግበት ወሳኝ መድረክ እንደሚሆንም ይጠበቃል።


የፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ አስተባባሪ በረከት ሲሳይ እንደገለጹት፤ ጉባኤው ፈጣን ዕድገት እያስመዘገበ ባለው ሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ የአፍሪካን የዲጂታል ገጽታና ይዘት ፈጠራ ላይ ትኩረት ያደርጋል ብለዋል።

በጉባኤ የቴክኖሎጂ ሥነ-ምኅዳር ፈጠራ፣ የአፍሪካ ታሪክና መፃኢ ተስፋዎች ላይ ጥራት ያላቸው የይዘት ሥራዎችን ለማስተጋባት አቅም የሚፈጠር አህጉራዊ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል።

ሁነቱ በአፍሪካ ሀገራትና በዓለም ዙሪያ የሚሰሩ ከ200 በላይ ተፅዕኖ ፈጣሪ የማህበራዊ ሚዲያ ግለሰቦች ተሰባስበው የሚመክሩበት መሆኑንም ተናግረዋል።

የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦቹ በዘላቂ ልማት፣ ዲጂታል አስተዳደርና የይዘት ፈጠራ አቅምን የሚያጎለብቱ የምክክርና የትውውቅ መርሃ ግብሮች እንደሚያካሄዱ አብራርተዋል።

በሰው ሰራሽ አስተውሎት ልምድና ተሞክሮ የሚለዋወጡበት፣ የአፍሪካን ዕድገት በዲጂታል ሥርዓት መግለጥ የሚያስችል እንዲሁም የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጠሪዎችን ከትላልቅ የንግድ ድርጅቶች ጋር የሚያገናኝ መድረክ መሆኑንም አንስተዋል።


የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ ፕሮጀክት አስተባባሪ ባዩሽ ማሞ በበኩላቸው፤፤ ጉባኤው እያደገ በመጣው የዲጂታል ዓለም የአፍሪካን የዲጂታል ሥነ-ምኅዳር ትብብርና ተወዳዳሪነት ለማጎልበት አቅም ይፈጥራል ብለዋል።

በአዲስ አበባ የዓድዋ ድል መታሰቢያ የሚካሄደው የአፍሪካ የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ ይፋዊ ምዝገባ በቅርቡ እንደሚጀመር አስታውቀዋል።

በዚህም የይዘት ፈጣሪዎች፣ ተፅዕኖ ፈጣሪዎችና ባለድርሻ አካላት ጉባኤውን የሚመለከቱ ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት በ www.asmis.org ድረ-ገጽን መከታተል እንደሚችሉ ገልጸዋል።

የአህጉሪቱን ዲጂታል መጻኢ የፈጠራ አቅምና እጣ ፈንታ በተሻለ ይዘት ለመቅረጽ ጉባአው ወሳኝ መሆኑን ተናግረው ታላላቅ የንግድ ተቋማትና ድርጅቶችም ለጉባኤው ስኬታማነት በአጋርነት እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026